Skip to main content

Posts

በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ስር የሚገኙ ክላስተር ማዕከላት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ናቸው

በሃዋሳ ከተማ ክሬሸር ክላስተር ማዕከል በኢ ኤም ቲ አይ የፈጠራ ስራ ማህበር ፓቶን የተሰኘ ጀልባ የሰራ ሲሆን ማህበሩ ከዚህ ቀደምም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ 58 ያህል የፈጠራ ስራዎችን አምርቶ ለገበያ አቅርቧል፡፡ የትራፊክ መብራት ፣የቆጮ ማቀነባበሪያ ማሽንና ፓቶን ጀልባ ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ኢ ኤም ቲ አይ የፈጠራ ስራ ማህበር የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን በመስራት በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ የሚያቀርብ ሲሆን ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የማህበሩ ስራ አስኪያጅና የፓቶን ጀልባ ፈጠራ ባለቤት ወጣት ኢንጂነር በረከት መስፍን ገልጻል ፡፡ በኢ ኤም ቲ አይ የፈጠራ ስራ ማህበር በወጣት ኢንጂነር በረከት መስፍን የተመረተው ፓቶን ጀልባ ስፋቱ 15 ሜትር በ4 ሜትር ነው ፡፡ ጀልባው በፀሐይ ብርሃን( Solar ) የሚሰራ ሲሆን በአንድ ጊዜ 60 ሰዎችን ማጓጓዝ የሚችል መሆኑን የፈጠራው ባለቤት ተናግሯል ፡፡ ፓቶን ጀልባ በአሁኑ የገበያ ዋጋ ግምቱ 1.8 ሚሊየን ብር ሲሆን ለ36 ያህል ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠር እንደሚችልም ታውቋል ፡፡ የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚና የፓርኮች ኦፕሬሽን አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ ዬተራ ሀዋሳን ጨምሮ በክልሉ ባሉት አራት የክላስተር ማዕከላት በማህበርና በግል ያሉ አነስተኛና መካከለኛ ደረጃ አንቀሳቃሾች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ያላቸው ሚና እየጎላ መምጣቱን ጠቅሰው በሙሉ አቅማቸው እንዲያመርቱ ከኮርፖሬሽኑ የሚጠበቀው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ፡፡

Ethiopian Airlines Inaugurates a second Aviation Academy Campus in Hawassa

Ethiopian Airlines Group, the largest aviation group in Africa, inaugurates a new aviation training center in the city of Hawassa. The new aviation training center in Hawassa will serve as the second campus for Ethiopian Aviation Academy and will currently be providing pilot trainee programs. The facility accommodates different types of classrooms, three training simulators, three aircraft parking and workshop hangars, trainees’ and instructors’ dorm rooms, a cafeteria and sports ground for various sport types.   Ethiopian Aviation Academy had been providing aviation trainings at its base campus in Addis Ababa to trainees from different parts of the world. The new training center will enable the academy to accommodate more trainees. Regarding the new Aviation Academy campus Ethiopian Airlines Group CEO Mr. Mesfin Tasew said “We are truly happy to see the inauguration of our Aviation Academy second training center in Hawassa. As Africa’s giant in the aviation industry, we are determine

አየር መንገዱ በሀዋሳ ከተማ ያስገነባው የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ማዕከል ተመረቀ

(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀዋሳ ከተማ ያስገነባው የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ማዕከል ተመርቆ ተከፈተ፡፡ ማዕከሉን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ መርቀው ከፍተዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉትም÷የሀዋሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአጭር ግዜ ውስጥ ተደራጅቶ ይህን ማሰልጠኛ ተቋም ማቋቋሙ የሚበረታታ ነው። ወደ ክልሉ የሚመጡ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎችና እንግዶች የዚህ አየር መንገድ ተጠቃሚ መሆናቸው በመግለፅ የተለያዩ ማስፋፊያዎች እንዲሰሩ ጠይቀዋል። የክልሉ መንግስትም ተቋሙ ለሚፈልገው ትብብር ከጎኑ እንደሆነ ማረጋገጣቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቆ፣የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስን ጣሰው፣ የሲዳማ ክልል የስራ ሃላፊዎችና የኢትዮጵያ አቬሽን አካዳሚ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

ከቤኒዚን ስርጭት ጋር ተያይዞ በከተማዋ ይስተዋል የነበረውን ሰልፍ ማስቀረት እንደተቻለ የሐዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ

  ከጥር 22 ጀምሮ በኮፖን ስርዓት ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን እስከ አሁን ባለው 80% የኩፖን ስርጭት መደረጉ ተገልጿል። ህብረተሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት ለመስጠት የማደያ ባለቤቶችን በማወያየት ጭምር ስራው መጀመሩን የገለጹት የሐዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ ወ/ሪት በላይነሽ ገዳ ናቸው። ሀላፊዋ አሰራሩን ወደ መስመር ለማስገባት በሚደረገው እንቅስቃሴ ተግዳሮት ቢኖረውም ለስኬታማነቱ መምሪያው ቁርጠኛ ሆኖ መጀመሩን ተናግረዋል። በያንዳንዱ ማደያ ስርዓት ለማስያዝ የባለሙያው ቁርጠኝነትን የገለጹት ሀላፊዋ አሁን ላይ ምንም አይነት ሰልፍ እስከማይኖር መደረሱን ጠቁመዋል። ህብረተሰቡ የባለቤትነት ሚናውን እስከሚወጣ ድረስም ይህ የተጠናከረ አሰራር በዘላቂነት የሚቀጥል መሆኑን ነው ወ/ሪት በላይነሽ የገለጹት። የቤንዚን ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን በመለየት ስርዓት ለማስያዝ በሚደረገው ጥረት የግል ሞተር ሳይክሎችም ልበብሬና መታወቂያ ይዘው በመቅረብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑንም ጠቁመዋል። ህጋዊ ያልሆኑ ሞተር ሳይክሎች ግን ለስራው አስቸጋሪ መሆናቸውን ነው ሀላፊዋ የገለጹት። በማደያ አካባቢ ያገኘናቸው ተጠቃሚዎች በበኩላቸው ከረጅም ጊዜ በኋላ ወደ ማደያ መድረስ እንደቻሉ ተናግረዋል። ይህ አሰራር ዘላቂ ሆኖ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

‹‹የፌዴራል ፕሮጀክቶች የካሳ ክፍያ ለከፍተኛ የወንጀል ድርጊት ምንጭ እየሆነ ነው›› የፍትሕ ሚኒስቴር

የፌዴራል መንግሥት በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በሚያካዷቸው የመሠረተ ልማት አገልግሎቶች ግንባታ፣ ለልማት ተነሽዎች የሚሰጠው የካሳ ክፍያ ለከፍተኛ የወንጀል ድርጊት መጋለጡ ተገለጸ፡፡ መንግሥት በመንገድ፣ በቴሌኮም፣ በውኃ፣ በኤሌክትሪክና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚገነባበት ወቅት ለልማት ለሚፈለግ ቦታ የሚደረገው የካሳ ክፍያ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ካሉ ወንጀሎች ዋነኛውና ትልቁ መሆኑን፣ በፍትሕ ሚኒስቴር በወንጀል የተገኘ ሀብት ምርመራና ማስመለስ ዳይሬክተር ወ/ሮ ፀጋ ዋቅጅራ ተናግረዋል፡፡ የካሳ ክፍያ መዘግየት፣ ካሳ የተከፈላቸው ግለሰቦች ማንነት በግልጽ አለመታወቅ፣ ክፍያው ለእነማን እንደተፈጸመ፣ እንዲሁም ‹‹የተከፈለበት አግባብ ሕግን መሠረት ያደረገ ነው ወይ?›› የሚለው ጉዳይ ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያስፈልገው የገለጹት ዳይሬክተሯ፣ ሕግ ያልተከተሉ አሠራሮች ለከፍተኛ የወንጀል ድርጊት እየተጋለጡ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በቀድሞው የተቀናጀ መሠረተ ልማት ማስተባበሪያ ኤጀንሲ፣ የ2013/2014 የክዋኔ ኦዲት ግኝት ሪፖርት አፈጻጸም ላይ ሰኞ ጥር 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አድርጎ ነበር፡፡ በመሠረት ልማት ገንቢ ተቋማት መካከል ያለውን ያልተናበበ አሠራር መፍትሔ ይሰጣል በሚል ከዓመታት በፊት ተቋቁሞ የነበረውና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠሪ የነበረው ኤጄንሲው፣ በ2014 ዓ.ም. እንደ አዲስ በተዋቀረው የአስፈጻሚ አካላት ከነበረበት አደረጃጀት ፈርሶ ወደ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር መካተቱ ይታወሳል፡፡ ለውይይቱ የተገኙት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ወንድሙ ሴታ (ኢንጂነር)፣ መሠረተ ልማት የሚገነቡ ተቋማት ተቀናጅተው ባለመሥራታቸው

የሀዋሳ ከተማ ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥና የጎብኚዎችን ቁጥር ለመጨመር በትኩረት እየሰራ መሆኑን የከተማዋ ፖሊስ መመሪያ አስታወቀ

በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሕብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለብልጽግና ጉዞ ስኬት በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ ውይይት መካሄዱን ሰምተናል