Skip to main content

Posts

ዓለም አቀፉ የአረንጓዴ ልማት ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ቢሮ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ

  ( ኢዜአ ) ዓለም አቀፉ የአረንጓዴ ልማት ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ቢሮ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በደን ልማትና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ያተኮሩ ተግባራትን በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱን ዛሬ በሀዋሳው የኃይሌ ሪዞርት የተፈራረሙት የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ገመዶ ዳሌ እና የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አያኖ በራሶ ናቸው። በስምምነቱ ወቅት ዶክተር ገመዶ ዳሌ በተለይ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዓለም አቀፉ የአረንጓዴ ልማት ኢንስቲትዩት ላለፉት 10 ዓመታት የኢትዮጵያን መንግሥት በተለያየ ደረጃ ሲደግፍ ቆይቷል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስትራቴጂ ከመቅረጽ ጀምሮ የቴክኒክ፣ የፋይናንስ እና የአቅም ግንባታ ድጋፍ በመስጠት ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አስታውሰዋል። አሁንም ከኮሪያ መንግሥት በተገኘ የ 9 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ የ 5 ዓመት ፕሮጀክት ተቀርፆ በዚህ ዓመት ወደ ትግበራ መገባቱን አመላክተዋል። ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር የተደረገው ይህ ስምምነትም የፕሮጀክቱ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ በአብዛኛው ፕሮጀክቱ በሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ በሆኑ ወረዳዎች የሚተገበር መሆኑን አስታውቀዋል። በአለታ ወንዶ፣ ሻሸመኔ እና አርቤጎና ወረዳዎች ውስጥ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ የተጎዳ 13 ሺህ ሄክታር መሬት እንዲያገግምና ወደ ምርታማነት እንዲመለስ የሚሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። እንዲሁም ያለውን የደን ሀብት መጠበቅና መንከባከብ፣ የህብረተሰቡን የኢኮኖሚና የገቢ ምንጭ አማራጮችን ለ

ጥላቻ እና ትውልድን ማጣላት፡- ቆይታ ከደራሲው ጋር

በማኅበራዊ ሚዲያ ወንጀል የሚፈጽሙ የውጭ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ እንደሚገኝ ተገለጸ

  የተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመጠቀም ወንጀል የሚፈጽሙ የውጭ ዜጎች ቁጥራቸው እየጨመረ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡ የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ አገር በሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የውጭ አገር ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች ከመሆኑ ባሻገር፣ ከግለሰብ እስከ ተቋማት የሚደርስ የማወናበጃ ሥልት የሚተገበርበት መሆኑን፣ በብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት እና የፋይናስ ደኅንነት አገልግሎት የተዋቀረው የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ በፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት የፋይናንስ ወንጀሎች ትንተና ኃላፊ አቶ ዮናስ ማሞ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ የማኅበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የሚደረገው የማጭበርበር ድርጊት ካለፉት ሁለት ዓመታት አንስቶ ሲፈጸም የቆየ ቢሆንም፣   ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰና ዓይነቱንም እየቀየረ መጥቶ በማኅበረሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል ብለዋል፡፡ ጉዳዩን ከስሩ ለማጥናት ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እና ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት የተወጣጣ ግብረ ኃይል   እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጾ፣ የኅብረተሰቡን የግንዛቤ ደረጃ በማየት በአገር ውስጥ ከሚገኙ ግለሰቦች ጋር በመመሳጠር የተለያዩ የማጭበርበሪያ ሥልቶችን የሚተገብሩ የውጭ አገር ዜጎች ቁጥራቸው መበራከቱን ማረጋገጡ ተመላክቷል፡፡ በተለይ በዚህ ዓይነቱ ወንጀል በብዛት ተጠቂ ሆነው የተገኙት ሴቶች ናቸው ተብሏል፡፡ የውጭ አገር ዜጎች የማኅበራዊ የትስስር ገፆችን በመጠቀም የረዥም ጊዜ መግባባት በመፍጠር፣ ‹‹ ዕቃ እ