በሲዳማ ክልል ያለውን ዕምቅ የቱሪዝም አቅም ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ -------------------------- በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያለውን ዕምቅ የቱሪዝም አቅም በተገቢው ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ፡፡ በክልሉ 33ኛውን የዓለም የቱሪዝም ቀን “ቱሪዝም ለገጠር ልማት በሚል መሪ ቃል” ተከብሯል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህን ወቅት እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ ባላት አቅም ልክ ተጠቃሚ አልነበረችም፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ከፍተኛ ዕሴት የሚጨምሩ ታላላቅ ፕሮጀክቶች በሀገር ደረጃ ተጀምረው በመጠናቀቅ ላይ ናቸው ያሉት አቶ ደስታ፣ ፕሮጀክቶቹ ወደ ክልሎች የሚደረግ የቱሪዝም ፍሰትን ከማሳደግ ረገድ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው እና በክልል ደረጃም በዘርፉ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ይፋ በማድረግ ወደ ስራ መገባቱንም ገልጸዋል፡፡ ክልሉ በርካታ የዓለምን ህዝብ ቀልብ የሚስቡ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም ሀብት መገኛ እንደሆነ ገልጸው፣ በቅንጅት እና በጋራ በመስራት በቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል፡፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጀጎ አገኘሁ በበኩላቸው፣ የአቃፊነት እና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነው የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ዕምቅ የቱሪዝም አቅም እንዳለው እና በዘርፉ የሚታዩ ውስጣዊ እና ውጫዊ ችግሮች ተለይተው በአጠረ ጊዜ ውስጥ ለመፍታት የሚያስችል ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር እንደተገባ ተናግረዋል፡፡ በተለይ በቱሪዝም መዳረሻዎች አከባቢ የሚታዩ ችግሮችን በመፍታት የቱሪዝም ዘርፉ ተገቢውን ጥቅም እንዲሰጥ በሚደረገው ጥረት በየደረጃው ያለ አመራር እና ባለድርሻ አካል ኃላፊነቱን በተገቢው መወጣት
የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል