Skip to main content

ሲዳማን ጨምሮ በርካታ ቡና ላኪዎች የገቧቸው ውሎች በመሰረዛቸው ለመላክ የታቀደው የቡና መጠን ቀነሰ


የአገር ውስጥ ግብይት ከዓለም ዋጋ የበለጠ መሆኑ አንደኛው ምክንያት ነው ተብሏል

ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝበት የቡና ወጪ ንግድ፣ በዚህ ዓመት ለመላክ ከታቀደው መጠን በታች አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ። ይህንን በማስመልከት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ባደረገው ጥናት፣ 181 ላኪዎች ወደ አውሮፓ አገሮች ቡና ሊልኩ 288 ውሎችን ቢፈጽሙም መላክ አልተቻለም ተብሏል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዘጋጅነት የግብርና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሰኞ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ተካሂዶ የነበረ ሲሆን፣ የቡናና ሻይ ባለሥልጣን ኃላፊዎችም ከቋሚ ኮሚቴው አባላት የቡና ወጪ ንግድን በሚመለከት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ማብራርያ ሰጥተዋል።

አብዛኞቹ በአውሮፓ የሚገኙ የቡና ገዥ አገሮች የገቡዋቸውን ኮንትራቶች በመሰረዛቸው፣ ተዘጋጅቶ የቀረበውን ቡና ባለመውሰዳቸውና በዋነኝነትም ዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ በመቀነሱ፣ ኢትዮጵያ ለመላክ ያቀደችው የቡና መጠን ሊቀንስ መቻሉን የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻፊ ዑመር በምክር ቤቱ ለተገኙት የቋሚ ኮሚቴ አባላት አብራርተዋል።

አቶ ሻፊ በማብራሪያቸው ባለሥልጣኑ ጥናቱን ባካሄደበት የበጀት ዓመቱ የመጀመርያ አምስት ወራት ለመላክ የታቀደው የቡና መጠን 137 ሺሕ ቶን ቢሆንም፣ የተላከው ግን 109 ሺሕ ቶን ቡና ነው ብለዋል። ቀሪው 28 ሺሕ ቶን ቡና በተሰረዙት ውሎች ውስጥ ታቅዶ እንደነበር አክለዋል።

‹‹ባካሄድነው ጥናት መሠረት የኮንትሮባንድም ሆነ ቡና የማጣት ችግር ሳይሆን፣ ለዚህ መንስዔው የዓለም ቡና ዋጋ መውረድ ነው፤›› ሲሉ አቶ ሻፊ የአገሮች የመግዛት አቅም ማነስን እንደ ትልቁ ችግር ገልጸዋል። ‹‹ቡናችን በስፋት ወደ አውሮፓ እንደ መሸጡ፣ በአውሮፓ ያሉ አገሮች ባጋጠማቸው ችግር ከዚህ በፊት የገቡትን ኮንትራት ሰርዘዋል፤›› ብለዋል።

ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የዓለም ቡና መሸጫ ዋጋ የዓለም አቀፍ የቡና መጠን መለኪያ በሆነው በፓውንድ 2.5 ዶላር ይሸጥ የነበረ ሲሆን፣ በዚህ ዓመት በአንድ ዶላር ወርዶ 1.5 ዶላር እየተሸጠ ነው። በኪሎ ግራም ደግሞ ወደ ሁለት ዶላር ወርዷል።

አቶ ሻፊ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ ላነሷቸው ጥያቄዎች ሲመልሱ፣ የቡና የአገር ውስጥ ግብይት ዋጋ ከዓለም አቀፍ ዋጋ የበለጠ መሆኑም አንደኛው ወደ ውጭ በተፈለገው መጠን ላለመላክ ምክንያት ነው ብለዋል። ‹‹በአገር ውስጥ የሚሸጥበት ዋጋ በጣም ከፍተኛ በመሆኑ፣ የዓለም ዋጋና የአገር ውስጥ ዋጋ ያለመናበብ ሌላኛው ችግር ነው፤›› ሲሉ አቶ ሻፊ ጠቁመዋል።

የቡና ወጪ ንግድ አፈጻጸም ከመጠን አኳያ ቅናሽ ቢያሳይም ያስገኘው የውጭ ምንዛሪ ላይ ግን ለጊዜው ማነስ ያልታየበት፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀርም የ80 ሚሊዮን ዶላር (14 በመቶ) ብልጫ ያለው መሆኑ ተጠቅሷል። እንደ አቶ ሻፊ ገለጻ፣ የቡና ገቢ እንደ መጠኑ ዝቅ ያላለበትን ምክንያትም ኢትዮጵያ የምትልከው ቡና ጥራት እያደገ በመምጣቱና ዋጋው ከፍ ያለ በመሆኑ ነው።

ኢትዮጵያ ባለፈው የበጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ካገኘችው 4.1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ውስጥ በቡና የተገኘው አንድ ሦስተኛውን የሚሸፍን ስለነበር፣ ቡና ለአገሪቱ ያለው የውጭ ምንዛሪ የማስገኘት አቅም ጥያቄ ውስጥ እንዳይገባ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ ሥጋታቸውን ገልጸዋል። ‹‹እንደተባለው ነገሩ አሳሳቢ ነው፣ ግን ችግሮችን ለመቅረፍ እየጣርን ነው፤›› ሲሉ አቶ ሻፊ የመሥሪያ ቤታቸውን ጥረቶች ዘርዝረዋል።

እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ አንደኛው ኮንትራቶቹ እንዳይሰረዙና የ181 ላኪዎች ቡና መውጣት እንዳለበት ግፊት ማድረግ ነው። በተጨማሪም አዳዲስ ገበያዎችን የመፈለግ ስትራቴጂ መንደፍ ይገኝበታል።

‹‹ነባር ገበያዎች ችግር ስላጋጠማቸውና አዳዲስ ገበያ ውስጥ መግባት ስላለብን እንደ ቻይና፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ታይዋን ዓይነት ገበያዎችን እየፈለግን እየገባን ነው። አንደኛ ገዥያችን ጀርመን ነበረች፣ አሁን የጀርመን የመግዛት አቅም እየወረደ ስለሆነ ቡናውን ወደ ሌላ ገበያ እንዲሄድ ለማድረግ ሰፊ ሥራዎች ተሠርተዋል፤›› በማለት ባለሥልጣኑ እያከናወናቸው ያሉትን ተግባራት አስረድተዋል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa