ቤተ ክርስቲያኗ ከ118 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚተገበር የልማት ስራ ይፋ አደረገች
አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን በተለያዩ ክልሎች ላይ ተግባራዊ የሚሆንና በ118 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የልማት ስራ ይፋ አደረገች፡፡
በደቡብ ክልል አራት ወረዳዎችና በሲዳማ ሦስት ወረዳዎችን እንዲሁም በኦሮሚያ ተልተሌን መዓከል ያደረገ ፕሮጀክት በይፋ ስራ የማስጀመር ስምምነት ተደርጓል ።
ተግባራዊ በሚደረጉት ፕሮጀክቶች ሦስት አብይ ተግባራት የሚከወን መሆኑን የተናገሩት በኮሚሽኑ የፕሮጀክቶች ዋና ዳይሬክተር አቶ ቢቂላ አበያ ፥ በሰላም ግንባታ ፣በሴቶች አቅም ማጎልበትና የምግብ ዋስት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ኮሚሽነር ዶክተር አበያ ዋቅወያ በበኩላቸው÷ ተቋሙ በሁሉም ክልሎች እየሰራ የሚገኝና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ270 ፕሮጀክቶች በላይ በተግባር ላይ እንደሚገኙም ነው የገለጹት ።
የ270 ፕሮጀክቶች አካል የሆኑ የተወሰኑ ፕሮጀክቶችን በሲዳማና ደቡብ ክልሎች ውስጥ ለመተግበር መፈራረማቸውን በመግለፅ በቀጣይም በሌሎችም ክልሎች ተግባራዊ የሚደረጉ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ለሦስት አመታት የሚቆይ ሲሆን ÷ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡ የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡ ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ
Comments
Post a Comment