Skip to main content

አቶ ብሩ ወልዴ ከኃላፊነታቸው ተነሱ

የቀድሞው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር የነበሩት ዶ/ር አለምነው መኮንን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ። ዶ/ር አለምነው የኢንተርፕራይዝ ልማቱ ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት፤ ተቋሙን ላለፉት 10 ወራት በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩ ወልዴ ከኃላፊነታቸው በመልቀቃቸው ምክንያት ነው።

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ባለፈው ዓመት መስከረም ወር በአዲስ መልክ ከተዋቀሩ የፌደራል የመንግስት መስሪያ ቤቶች አንዱ ነው። አዲሱ ተቋም በአዋጅ የፈረሰው የፌደራል አነስተኛ እና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኤጀንሲ መብት እና ግዴታዎች ተላልፈውለታል።

መስሪያ ቤቱ በአዲስ መልክ ከተዋቀረ ከአራት ወራት በኋላ በዋና ዳይሬክተርነት የመምራት ኃላፊነት የተረከቡት፤ የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽንን ከምስረታው ጀምሮ በዋና ስራ አስኪያጅነት ሲያስተዳድሩ የቆዩት አቶ ብሩ ወልዴ ነበሩ። አቶ ብሩ እስከ ትላንት ጥቅምት 2፤ 2015 በስራ ገበታቸው ላይ እንደነበሩ የስራ ባልደረቦቻቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የዋና ዳይሬክተርነት ኃላፊነታቸው “በገዛ ፍቃዳቸው” የለቀቁት ከዛሬ ጥቅምት 3፤ 2015 ጀምሮ መሆኑን አቶ ብሩ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። አቶ ብሩ ለዚህ ውሳኔ የበቁት “በግል ምክንያት” መሆኑን ከመግለጽ ባሻገር በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የዋና ዳይሬክተሩን ከኃላፊነት መልቀቅ የኢንተርፕራይዝ ልማት መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታህ የሱፍ አረጋግጠዋል። በተሰናባቹ ኃላፊ ምትክ ዶ/ር አለምነው መኮንን መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለተቋሙ መድረሱንም ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተፈረመ ደብዳቤ መሾማቸው የተገለጸው ዶ/ር አለምነው፤ የቀድሞው ብአዴን ጽህፈት ቤት ኃላፊ ነበሩ። የብአዴን እና የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት ዶ/ር አለምነው፤ በኢህአዴግ የመጨረሻ ዓመታት ስማቸው በጉልህ ከሚነሱ የአማራ ክልል አመራሮች አንዱ ነበሩ።

ዶ/ር አለምነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ በሚኒስትር ማዕረግ የቀድሞው የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ሆነው በሚያዚያ 2010 ዓ.ም ተሾመው ነበር። በአሁኑ ወቅት “የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ” የሚል ስያሜ በያዘው በመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ በኃላፊነት የቆዩት ግን ለሰባት ወራት ያህል ብቻ ነበር።

የቀድሞው ገዢ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ቀጣይ መዳረሻቸው የሆነው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አማካኝነት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው በህዳር 2011 ዓ.ም የተሾሙት አለምነው፤ በዚሁ የኃላፊነት ቦታቸው ላይ እያሉ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ለመስራት ወደ ቻይናው ፔኪንግ ዩኒቨርሲቲ አቅንተዋል። ባለፈው ግንቦት ወርም ከዩኒቨርስቲው የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በ“theoretical economics” አግኝተዋል።

አዲስ ዋና ዳይሬክተር ያገኘው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ተጠሪነቱ ለኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ነው። ይህ የመንግስት ተቋም የሚኖሩትን ስልጣን እና ተግባራት በተመለከተ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ እንደሚወጣ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ቢገልጽም፤ እስካሁን ተግብራዊ አልሆነም። ተቋሙን የሚመለከተው ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መላኩን እና በቅርቡ ይጸድቃል ብለው እንደሚጠብቁ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አብዱልፈታህ የሱፍ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa