Skip to main content

Posts

Showing posts from September, 2022

የኢትዮጵያ ቡና በጥራት፣ በተወዳዳሪነትና በዋጋ አስደናቂ ውጤት እየተመዘገበበት ነው

 የኢትዮጵያ ቡና በጥራት፣ በተወዳዳሪነትና በዋጋ አስደናቂ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን በኢትዮጵያ የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ አስተባባሪ ገለጹ። በመጀመሪያውና ሁለተኛው የባለ ልዩ ጣዕም (የካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ) ውድድር የኢትዮጵያ ቡና አስደናቂ ውጤት የተገኘበት መሆኑ ይታወቃል። የካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ሶስተኛው ውድድር የቡና እና ሻይ ባለስልጣን ከአሊያንስ ኮፊ ኤክሰለንስና የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤይድ) ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን የኢትዮጵያ ቡና አሸናፊ ሆኗል። በኦንላይን ጨረታ በተከናወነው መርሃ ግብር አንድ ኪሎ ቡና 884 ዶላር ከ10 ሳንቲም ወይም 47 ሺህ 236 ብር ከ23 ሳንቲም ተሽጧል። በዚህም የባለ ልዩ ጣዕም ቡና ቅምሻ ውድድር ጥራቱ የተጠበቀ ቡና ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መጥቷል። ባለፈው አመት በተካሄደው ውድድር ከ22 አገራት 170 ገዥዎች ተመዝግበው የኢትዮጵያን ቡና ለ11 ሰአታት በመጫረት አንድ ኪሎ ግራም ቡና 47 ሺህ 236 ብር ከ23 ሳንቲም ተሽጧል። የኢትዮጵያ ቡና በውድድሩ በሁሉም መልኩ የዓለምን ቀልብ እየገዛ መሆኑን የገለጹት በኢትዮጵያ የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ አስተባባሪ ቅድስት ሙሉጌታ፤ የኢትዮጵያ ቡና በጥራት፣ በተወዳዳሪነትና በዋጋ አስደናቂ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል። በካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ መሳተፍ የቡና ገዥዎች የውድድሩ አሸናፊ የሆነው አምራች አርሶ አደር ወደ ሚገኝበት አካባቢ ሄደው እንዲያበረታቱና ሌሎችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። በሦስተኛውን ዙር ውድድድር አሸናፊ የሆኑት አርሶ አደር ለገሠ በጦሳ፤ 1 ኪሎ ግራም ቡና 47 ሺህ 236 ብር በመሸጥ በድምሩ 479 ኪሎ ግራም 22 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር መሸጥ ችለዋል። ከ23 አገራት የተወጣጡ 170 ገዢዎች ተሳታፊ በ

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ በአዲሱ የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ዙሪያ ለመንግስትና ለግል ትምህርት ቤቶች የማስተዋወቂያና የማስጀመሪያ ስልጠና መስጠት ጀመረ

  በሲዳማ ብሔራዊ ክልል የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ በአዲሱ የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ዙሪያ ለመንግስትና ለግል ትምህርት ቤቶች የማስተዋወቂያና የማስጀመሪያ ስልጠና መስጠት ጀምሯል:: የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ማስተዋወቂያና ማስጀመሪያ ስልጠናው በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ለሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች የሚሰጥ ይሆናል:: ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚሰጠው በዚህ ስልጠና ሁሉም መምህራን፣ ር/መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የትምህርት ባለሞያዎችም የሚሳተፋ ይሆናል:: የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ በራሳ ዛሬ በሐገራችን በትምህርት ስርዓቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በተዘጋጀው የስርዓተ ትምህርት የመማሪያና ማስተማሪያ መፅሐፍት ክለሳ ዙሪያ የማስተዋወቂያ እና የማስጀመሪያ ስልጠና በክልል ደረጃ በሐዋሳ ከተማ መሰጠት መጀመሩን ገልፀዋል:: የስልጠና መድረኩን በንግግር ባስጀመሩበት ወቅት በትምህርት ራሳቸውን እና ዜጎቻቸውን የገነቡ ሀገራት ታላቅ ሀገር መሆን ችለዋል ያሉት አቶ በየነ በራሳ በሁሉም ዘርፍ ብቁ ሀገር ለመገንባት የትምህርት ስርዓትን ማሻሻል እና ለትምህርት ስራ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያሻል ብለዋል:: ይህን ታሳቢ ባደረገው የሀገራችን በአዲሱ የስርዓተ ትመህርት ክለሳ መነሻ በክልላችን ይተዘጋጁ መፃሀፍቶች በህትመት ሂደት ላይ ይገኛሉ ያሉት የትምህርት ቢሮ ኃላፊው በአዲሱ አመት በሙሉ አቅም ወደ ትግበራ እንደሚገባም አመላክተዋል:: ስልጠናው የትምህርት ማህበረሰቡን በ2015 ዓም ተግባራዊ በሚሆነው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መነሻ በክልል ደረጃ ከተከለሱ መፃህፍት ጋር ለማስተዋወቅ ያልመ መሆኑን የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ ዳንኤል ገልፀዋል:: አንድን ሀገር ወደ

የማር አምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ

የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ለግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ፡፡ በዚህም የአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ የውጭ ምንዛሪን ለማስገኘት በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎችን የመደገፍ ተግባራትንም እያከናወነ ይገኛል ፡፡ ለዚህም በይርጋዓለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ከሚገኙት የግብርና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች መካከል አንዱ ሀሮ የማር ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የዚሁ ማሳያ ነው ፡፡ ፋብሪካው ንፁህ የተፈጥሮ ማር እንዲያገኝ ከአካባቢው ንብ አርቢዎች ጋር የገበያ ትስስር ከመፍጠር በተጓዳኝ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በመዘርጋት ምቹ ሁኔታን ፈጥሮላቸዋል ፡፡ ኮርፖሬሽኑ ከልማት አጋር ድርጅት ጋር በመተባበር በክልሉ ሀሮሬሳ ወረዳ ለሚገኙ 3 የማር አምራች ማህበራት ባህላዊና ዘመናዊ የማር ማምረቻ ቀፎዎችን ያሰራጨላቸው ሲሆን የማር ምርታማነትንና ጤናማነትን የሚጠብቁ ሌሎችንም መርጃ ቁሳቁሶችን አበርክቶላቸዋል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከጂ አይ ዜድ የልማት ተራድኦ ድርጅት ከሳንቫዶ የአቮካዶ ዘይት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ጋር በጋራ በመሆን ከ200 በላይ ለሚሆኑ ለማር አምራች አርሶ አደሮች ተገቢውን ስልጠናና ድጋፍ እያደረገ በመሆኑ አሁን ላይ በክልሉ ያለው የማር ምርትና የምርታማት አቅም በቂ በመሆኑ በይርጋዓለም የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተዘረጋው የመሰረተ ልማት አቅርቦትም አስተማማኝ በመሆኑ በዘርፉ ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው አልሚ ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ኮርፖሬሽኑ ጥሪውን ያቀርባል ፡፡

ግን ለምን?

በአገራችን በሰሜኑ ክፍል ብቻ ሳይሆን፤ በሁሉም ክፍሎች በሚባል ደረጃ በተለያዩ አከባቢዎች እየሆኑ ያሉትን ጸረ ሰላም ተግባራት፣ ግጭቶች፣ ግድያዎች እና ህገ ወጥነቶችን፤ ልክ እንደ ማንኛውም የእለት ተእለት እንቅስቃሴዎች፣ ልክ እንደ የመማር   የማስተማር፣ ልክ እንደ አምልኳ ተግባራት፣ ልክ እንደ ንግድ፣ ልክ እንደ ስፖርት እግር ኳስ ውድድር እንደማየት እና መስማት ወዘተ ምንም የማይመስሉን፣ የትራፊክ አደጋ ያህል እንኳን የማያሳስቡን ለምንድነው? ለምንድነው አንዱ በሌላው ላይ ጨክኖ ሲገዳደል፣ አንዱ ሌላውን ሲያፈናቅል፣ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ነፍስ አጥፍቶ ሀብትና ንብረት አውድሞ ስሳለቅ ልክ እንደ ፊልም ከማየት ሌላ እየሆነ ያለው ነገር የማይገደን? ለምንድነው፤ የአገሪቱ መሪዎች እና የህዝብ ተወካዮች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሽማግሌዎች፣ ወዘተ፤ አገሪቱ በተለያዩ አከባቢዎች በሚፈጸሙ ግጭቶች በሰላማዊ ዜጎች ደም ስትጥለቅለቅ ዝም ብለው ሲያዩ እያየን ምንም የማንለው? ለምንድነው፤ የማህበራዊ ጉዳዮች አንቂዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ምሁራን፣ ወዘተ፤ ከማህበራዊ እና ሀይማኖታዊ እሴቶቻችን ባፈነገጠ መልኩ ግጭቶችን ስቀሰቅሱ ምንም እንዳልሆነ አድርገን የምናያቸው እና የምንከተላቸው?     ለምንድነው የግጭት ተዋኒያን የሆኑት የመንግስት እና የተቃዋሚ ሃይሎች፣ በየአከባቢው የሚያደርጉትን ግጭት አቁመው ወደ ሁሉ አቀፍ የሰላም ድርድር እንዲመጡ እና በአገሪቱ ሰላም እንድመጣ ሰላማዊ መንገዶችን ተጠቅመን የማንጠይቀው? ለምንድነው በአገሪቱ ሰላም እንዳይሰፍን የምሰሩትን፤ የመንግስት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ግለሰቦችን እና ሌሎች አካላትን በጽኑ በመቃዎም እና በማጋለጥ ለአገሪቱ ሰላም ዘብ የማንቆመው? ለምንድነው፤ አገሪቱ የእርስበርስ ግጭ

Ethiopia Sidama Coffee Breaks Cup of Excellence Record at $400.50/lb

The top-scoring coffee in the 2022 Ethiopia Cup of Excellence (CoE) fetched $400.50 per pound during a public auction last week, breaking the record for the highest price ever paid for a CoE-winning green coffee. Half of the 1,058-pound lot of coffee, grown by farmer Legesse Botasa Dikale in Ethiopia’s renowned Sidama region, was purchased by Chinese company LNK Coffee Trading. The other half of the natural-process lot was purchased for $400 per pound by Saza Coffee in Japan and Orsir Coffee in Taiwan. The purchases represent new all-time price highs for the 20-plus-year-old competition and auction program , and CoE organizers believe it is the highest price ever recorded for an Ethiopian green coffee. The previous CoE record was for a honey-process Gesha coffee in Costa Rica in 2018 that fetched $300.09. The second-place coffee in the Ethiopia CoE — an anaerobic-process coffee from farmer Kenean Assefa Dukem, also from Sidama — earned $189.10 per pound from winning buyer Sulalat Co

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ልማት ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ይገኛል

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ልማት ንቅናቄ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ የቡና ምርት ላይ በከፍተኛ መነቃቃት ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን የገለፁ ሲሆን በዚህም በጥራት ከፊት መሰለፉን ገልፀዋል። የቡናን ምርት ለማስፋትና ጥራት ለመጨመር በግብርና ባለሙያ ለአርሶ አደሩን እየተደረገ ያለው እገዛ እንደሚጠናከር የገለፁ ሲሆን አርሶ አደሩ የግብርና ባሉሙያ የሚያሳያቸው አቅጣጫ እንዲከተሉ አሳስበዋል። የፍራፍሬ ምርት የማስፋትና ጥራት የመጨመር ስራ እየተሰራ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የፍራፍሬ ምርታማነት በማሳደግ የአርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል። የእርሻ እና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አቶ መስፍን ቃሬ እንደገለፁት የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ የቡና፣ ፍራፍሬ እና ቅመማቅመም ጥራት የማሳደግና የማስፋት ስራ በመስራቱ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን የገለፁ ሲሆን በቡና ምርት በጥራት ተወዳዳሪ መሆን መቻሉን ገልፀዋል። አክለውም የክልላችን የቡና ምርት ለአገራችን የውጭ ምንዛሬ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን ገብያቸውን በቡና ምርት ላይ ያደረጉ የክልላችን አርሶ አደሮች የገቢ ምንጫቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ገልፀዋል። ለይርጋዓለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍራፍሬ ምርት እየቀረበ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን በዚህም አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን በመግለፅ የፍራፍሬ ምርትን ከዚህ በተሻለ ደረጃ ለማስፋፋት እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል። በንቅናቄው መድረክ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ዘርፍ