Skip to main content

በሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አከባቢዎች የሚከሰቱትን ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያስችላል የተባለለት የሰላም ኮንፌራንስ በሐዋሳ ከተማ እንደሚካሄድ ሰምተናል

 


ሰሞኑን በሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አንዳንድ ቀበሌያት ተከስተው በነበረው ግጭቶች በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወሰ ሲሆን፤ ባለፉት ጥቅት ቀናት ይህንን በተመለከተ በአከባቢው ሰላለው አጠቃላይ የጸጥታ ሁኔታ እና በቀጣይነት ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ በመደረግ ላይ ባሉት ተግባራት ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት አንዳንድ መረጃዎችን ለአንዳንድ የክልሉ የሚዲያ አውታሮች ስሰጡ ተመልክተናል።

ባለፈው ሳምንት የተከሰተው እና በሰው ነፍስ እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰው ግጭት በተለየ ሁኔታ እንደሚባለው በህዝቦች መካከል የተነሳ ሳይሆን፤ በኦሮሚያ ክልል የሚቀሳቀሱ የታጠቁ ሃይሎች በግልጽ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሲዳማ ልዩ ሃይል በኦሮሚያ መሰማራቱን በመቃዎም እና ለዚሁ የበቀል እርምጃ በሲዳማ ህዝብ ላይ እንደሚወስዱ በአደባባይ ካዛቱ በሃላ የፈጸሙት ነው።

ይህንን የአሽባሪ ቡድን ተግባር በመጀመሪያ ደረጃ የሁለቱም ክልል መንግስታት በአደባባይ ማውገዝ እና ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ቃል መግባት ሲገባቸው፤ ምንም ሳይሉ ማለፋቸው ብሎም በአጠቃላይ፤ ከመንግስትም ሆነ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በግዳዩ ላይ የተባለ ነገር አለመኖሩ በርካታ፣ በተለይ የሲዳማን ምሁራንን ማስቆጣቱ ይታወሳል።  

ያህም ሆነ ይህ ከቆይታ በሃላም ቢሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሰሞኑን በዳዬ ከተማ ውይይት ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን፤ በወይይቱም ላይ በአጎራባች አከባቢዎች በተደጋጋሚ የሚከሰቱትን ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፋታታ ያስችላል የተባለለት ሰነድ ላይ ውይይት መደረጉ እና ከስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል።

ለወራንቻ ድረገጽ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ፤ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ አርሲ ዞን እና በሲዳማ ክልል የድንበር ሰላምን ለማስፈን የተዘጋጀ የጋራ ስምምነት ስነድ በድንበር አከባቢ በተደጋጋሚ ግጭቶች በሚከሰቱባቸው አከባቢዎች የሚኖሩ የሁለቱም ክልል ህዝቦች የሰላም እና የእርቅ ኮንፌራንሳችን እንዲያካህዱ የሚያደርግ ነው።

ከዚህም ባሻገር ግጭት በሚቀሰቅሱ እና በግጭት ላይ በሚሳተፉ አካላት ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሁለቱም ክልል አከላት እርምጃ ለመውስድ መስማማታቸው የተነገረ ሲሆን፤ ለዚህም እንድረዳ ከሁለቱም ክልሎች የተወጣጣ አንድ የምርመራ ቡድን መቁቋሙን፤ የየአከባቢዎቹ የፖለቲካ አመራሮች ዘላቂ ሰላም ማምጣት በሚያስችሉ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እንዲያደርጉ መወሰኑ እና በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ ከአጎራባች ቀበሌያት የተወጣጡ ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት መሪዎችን ያካተተ የሰላም ኮንፌራንስ በሐዋሳ ከተማ እንዲደረግ ከስምምነት ላይ መደረሱ ተሰምቷል።

በቀጣይነትም የሰላም እና የእርቅ ኮንፌራንሶች በየቀበሌያቱ የሚካሄዱ ሲሆን፤ በወንጀል ላይ ተሳትፎል ተብሎ የተጠረጠሩት በህግ ስር ሆነው የማጣራት ስራ እንደሚሰራባቸው እና ወንጀለኞችን ከአንዱ ክልል ወደ ለሌላኛው ክልል አሳልፎ ለመስጠት ከስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል።

ግጭቱን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በኩል አንዳንድ እርምጃዎች መወሰዳቸው የተሰማ ሲሆን፤ ግጭቱ እንዳከሰት መስራት ያቻሉ እና ቸልተኝነትን አሳይቷል የተባሉ አመራሮች ከሃላፍነታቸው ላይ መነሳታቸው ተነግሯል። ነገር ግን ከሲዳማ ክልል በኩል ተመሳሳይ እርምጃዎችን አለመወሰዳቸው ተገልጿል።

በሲዳማ እና ኦሮሚያ አጎራባች አንዳንድ አከባቢዎች አልፎ አልፎ ግጭቶች መከሰታቸው አዲስ ነገር ባይሆንም፣ ባልፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በተደጋጋሚ መከሰታችው እና በተለይ ባለፈው ሳምንት በግጭቱ ላይ የተሰተፉት ሃይሎች የታጠቁ እና በሚሊቴር ሳይንስ የተደራጁ መሆናቸው ልዩ ያደርገዋል ተብሏል።

ከዚህም ባሻገር እነዚህ የተጠቁ ሃይሎች ከአጎራባች አከባቢዎች አለመሆናቸው እና ምንም አይነት ግጭት ሳይኖር በቀጥታ በሲዳማ አርሶ አደሮች እና በነዋሪዎች ላይ በዘፈቀደ ጥቃት የተፈጸመ መሆኑ አሳሳቢነቱን ከፍ አድርጎታል።

የሁለት ክልል መንግስታት በአመራሮች ደረጃ የሚያደርጉትን እከከኝ ልከክህ ግኙኝነትን ብቻ በህዝቦች መካከል ሰላምን ማምጣት ስለማይችል ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት በሚያስችሉ አቅጣጫዎች ላይ ትኩረት ስጥተው መሰራት ይጠበቅባቸዋል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa