Skip to main content

Posts

Showing posts from May, 2022

በዘንድሮውን የካፕ ኦፍ አክስለንሲ ኢትዮጵያ ውድድር፤ 13 የሲዳማ ቡና አብቃዮች ከ40 ምርጥ አብቃዮች መካከል መሆናቸው ታወቀ

በዘንድሮውን የካፕ ኦፍ አክስለንሲ ኢትዮጵያ ውድድር፤ 13 የሲዳማ ቡና አብቃዮች ከ40 ምርጥ አብቃዮች መካከል መሆናቸው ታወቀ። የዘንድሮ በቡና ጥራት ውድድር አርባ ምርጥ የቡና አብቃኖች ስም ዝርዝር ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ የሲዳማ ቡና አብቃይ የሆነው እና ከሲዳማ ክልል የቦና ዙሪያ ወረዳ በውድድሩ የተሳተፈው ቡና አብቃይ ካላ አበበ ሄዊሳ ዊቾን ጨምሮ 13 የሲዳማ ቡና አብቃዮች የዘንድሮውን የቡና ጥራት ውድድር በብሄራዊ ደረጃ በምርጥ ቡን ኣብቃይነት ተካተው አይተናል።  በውድድሩ ተሳትፎ ለሆኑት የሲዳማ ክልል ቡና አብቃዮች መልካም እድል እንመኛለን።

Sidaamunna Oromote qoqqowubba qasiisotenni xaaddanno qooxeessuwara ka’annota ga’labbote qarrubba tirate hasaawu bare harinsanni hee’noonni

  (IPU/Bakkalcho Gaazeexa) Sidaamunna Oromiyu qoqqowubba qasiisotenni xaaddanno qooxeessuwara sa’e sa’e kalaqantannota ga’labbote qarrubba sufino garinni tirate dandiinanni garinni hasaawu bare techo Hawaasa ha’rinsanni hee’noonni. Hasaawu ba’re lamenti qoqqowubba qasiisotenni xaaddanno qooxeessuwara saada allaa’linanni basenna wolootta korkaatta kaiminni kalaqantannota ga’labbote qarrubba gutunnita ikkitino gaance tiratenna araaru hayyonni qarrubba sufino garinni tirate dandiisiissanno sumiimmeno assinanni yine agarranni. Hananfoonni hasaawu ba’rera gobbate geerrinna hajo la’annonsa bissa beeqqitanni afantannota ‘EBC’ odeessino.

እውቁ ኬንያዊ አትሌት ፖል ቴርጋት ሀዋሳ ከተማ ገባ

  አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) እውቁ የኬንያ አትሌት ፖል ቴርጋት የኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣቶች የኦሎምፒክ ውድድርን ለመታደም ሀዋሳ ከተማ ገብቷል፡፡ አትሌት ፖል ቴርጋት በሲዳማ ክልል አዘጋጂነት ከግንቦት 21 እስከ ሰኔ 4/2014 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደውን 1ኛውን የኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣቶች የኦሎምፒክ ውድድርን በክብር እንግድነት ለመታደም ነው ሀዋሳ ከተማ የገባው፡፡ በተጨማሪም የአፍሪካ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ዋና ጸሐፊ አቶ አህመድ ጋሽም፣ የብሩንዲ ኦሎምፒክ ፕሬዚዳንትና የአፍርካ ኦሎምፒክ ሥራ አስፈፃሚ፣ የኬንያ ኦሎምፒክ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ዞን 5 ዋና ጸሐፊ፣ ዶክተር ቶኒ የደቡብ ሱዳን የኦሎምክ ፕሬዝዳንት፣ አቶ ልዑል ፍሰሃ የኤርትራ ኦሎምፒክ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ዞን 05 ዓቃቤ ንዋይ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም ሀዋሳ ገብተዋል። በተመሳሳይ የኦሎምፒክ ውድድሩን ለመታደም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፌጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ሀዋሳ ከተማ መግባታቸው ታውቋል፡፡ እንግዶቹ ሀዋሳ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የሲዳማ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ፥ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ጋር በመሆን አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣቶች የኦሎምፒክ ውድድር በነገው ዕለት በሲዳማ ክልል አዘጋጅነት በሀዋሳ ከተማ ይጀመራል።

በሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አከባቢዎች የሚከሰቱትን ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያስችላል የተባለለት የሰላም ኮንፌራንስ በሐዋሳ ከተማ እንደሚካሄድ ሰምተናል

  ሰሞኑን በሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አንዳንድ ቀበሌያት ተከስተው በነበረው ግጭቶች በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወሰ ሲሆን፤ ባለፉት ጥቅት ቀናት ይህንን በተመለከተ በአከባቢው ሰላለው አጠቃላይ የጸጥታ ሁኔታ እና በቀጣይነት ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ በመደረግ ላይ ባሉት ተግባራት ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት አንዳንድ መረጃዎችን ለአንዳንድ የክልሉ የሚዲያ አውታሮች ስሰጡ ተመልክተናል። ባለፈው ሳምንት የተከሰተው እና በሰው ነፍስ እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰው ግጭት በተለየ ሁኔታ እንደሚባለው በህዝቦች መካከል የተነሳ ሳይሆን፤ በኦሮሚያ ክልል የሚቀሳቀሱ የታጠቁ ሃይሎች በግልጽ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሲዳማ ልዩ ሃይል በኦሮሚያ መሰማራቱን በመቃዎም እና ለዚሁ የበቀል እርምጃ በሲዳማ ህዝብ ላይ እንደሚወስዱ በአደባባይ ካዛቱ በሃላ የፈጸሙት ነው። ይህንን የአሽባሪ ቡድን ተግባር በመጀመሪያ ደረጃ የሁለቱም ክልል መንግስታት በአደባባይ ማውገዝ እና ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ቃል መግባት ሲገባቸው፤ ምንም ሳይሉ ማለፋቸው ብሎም በአጠቃላይ፤ ከመንግስትም ሆነ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በግዳዩ ላይ የተባለ ነገር አለመኖሩ በርካታ፣ በተለይ የሲዳማን ምሁራንን ማስቆጣቱ ይታወሳል።   ያህም ሆነ ይህ ከቆይታ በሃላም ቢሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሰሞኑን በዳዬ ከተማ ውይይት ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን፤ በወይይቱም ላይ በአጎራባች አከባቢዎች በተደጋጋሚ የሚከሰቱትን ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፋታታ ያስችላል የተባለለት ሰነድ ላይ ውይይት መደረጉ እና ከስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል። ለወራንቻ ድረገጽ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ፤ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ አርሲ ዞን እና በሲዳማ ክልል የድንበር ሰላምን ለማስፈን የተዘጋ

የዳቶና ጨፌ የአስፓልት መንገድ ስራ ግንባታ ተጀመረ

  የዘመናት የህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ የነበረውን ይህን የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ያስጀመሩት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረ / ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ ናቸው። ከንቲባው በንግግራቸው የመንገዱ መገንባት የህዝቡን የልማት ጥያቄን ከመፍታትም ባሻገር ለአካባቢው ህብረተሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በየአመቱ በክረምት ወቅቶች አካባቢው ለከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እንደሆነ በመገንዘብም የመንገዱ ግንባታ ከወዲሁ መከናወን መጀመሩንንም ነው ከንቲባው የገለፁት። ግንባታውን በጥራትና በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስተዳደሩ የበኩሉን ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግም ከንቲባው ጠቁመዋል። አቶ ታሪኩ ታመነ የሐዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ም / ኃላፊና የማስፈጸም አቅም ግንባታና የአካባቢ ልማት ዘርፍ ኃላፊ በቱላ ክ / ከተማ በጨፌና በዳቶ ቀበሌዎች 2.8 ኪ . ሜ በ 339 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ይከናወናል ብለዋል። ይህ ግንባታ ቀደም ብሎ የመንገድ ከፈታ፣የውሐ፣የቴሌ መስመሮች የተጠናቀቀ መሆኑን ያስታወሱት ሀላፊው በዚህም በዛሬው ዕለት ግንባታው በይፋ ተጀምሯል ብለዋል። ለሚገነባዉ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራም ቀደም ተብሎ የጎርፍ መውረጃ ቦዮች መገንባታቸውንም ነው አቶ ታሪኩ ያስረዱት። ይህ በዛሬው ዕለት በይፋ በዩኤን ዲፒ በጀት የተጀመረው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራም በአንድ ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል በማለት ሀላፊው አያይዘው አስረ