Skip to main content

Posts

Showing posts from February, 2022

“ከዚህ በኃላ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ በውሸት ሪፖርት መቀለድ አይቻልም”፦ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

  “ከዚህ በኃላ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ በውሸት ሪፖርት መቀለድ አይቻልም”፦ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ********************** ከዚህ በኃላ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ በውሸት ሪፖርት መቀለድ አይቻልም ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ። ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን ያሉት የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሥራ ዕድል ፈጠራ የስትሪንግ ኮሚቴ የ7 ወር አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በንግግራቸው አንድ ሰው ትምህርት የሚማረው በእውቀትና በክህሎት ሥራውን ለመስራት እንዲረዳው እንጂ በመንግሥት መሥሪያ ቤት ልቀጠር ነው ብሎ መሆን የለበትም ብለዋል። ማንም ሰርቶ ነው ሀብት የሚያፈራው ለዚህም ወጣቱ ሰርቶ እንዲለወጥ ስራ መፍጠር ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በክልላችን ሥራ የሚፈልጉ ወጣቶች ቁጥር በርካታ በመሆኑ ወጣቱን ቀጥሮ ብቻ ስራ ማስያዝ ስለማይቻል የሥራ ዕድል መፍጠር ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም ብለዋል። በመሆኑም ወጣቶችን በተለያዩ አደረጃጀት በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በትምህርትና ወዘተ.. በማዋቀር ለወጣቶች ሥራ መፍጠር ያስፈልጋል በማለትም ከዚህ በኃላ በውሸት ሪፖርት እየዋሹ መኖር እንደማይቻል አጠንክረው አንስተዋል። በዚህ መድረክ ላይ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርና የስትሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ የሥራ፣ የክህሎትና ኢንተርፕራዝ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀገረፅዮን አበበ፣ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን ከሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት የገኘነው መረጃ አመልክቷል።   EBC

በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 28 በርሜል (6160) ቤንዚን ተያዘ፤

  በመሐል ክ/ ከተማ አስተዳደር የተያዘው 6160 ሊትር (28)ቤርሜል ቤንዚን በህገ_ወጥ መንገድ ወደ ወረዳ ለማጓጓዝ ታስቦ የነበረ መሆኑን የገለጹት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ተወካይ አቶ አዳነ አየለ ናቸው። አቶ አዳነ ይህ ህገወጥ ቤንዚን በመናኸሪያ፣ በምስራቅ ክ/ከተማና በሌሎችም ክ/ከተሞች በጀሪካንና በሃይላንድ የተገኘ መሆኑን ገልጸዋል። ከነዳጅ አስተዳደርና አያያዝ ጋር ተያይዞ የሚነሳን ቅሬታ ለመፍታት መምሪያው ከጸጥታ ሀይል ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትል መያዝ እንደተቻለ ነው አቶ አዳነ ያስረዱት። ህገወጥ ስራ ከህብረተሰቡ እንደማይሰወር የተናገሩት አቶ አዳነ ለማደያ ባለቤቶችና አስተዳዳሪዎች፣የተሽከርካሪ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች፣ ሱቆችና ጋራዥ ቤቶች እንዲሁም በየመንገዱ ቤንዚን ይዘው የሚቆሙ ወጣቶች ሁሉ ከህገወጥ አሰራር ሊታረሙ እንደሚገባ ተናግረዋል። በዘርፉ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት በከተማዋ የተቋቋመ ቡድን መኖሩን የገለጹት አቶ አዳነ ቡድኑ ተገቢውን ክትትል እያደረገ መሆኑን ሲጠቁሙ ህጋዊ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም በመግለፅ ነው። የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮ/ር ደረሰ ቡሳሮ በከተማዋ ካሉ 15 ማደያዎች አንዱ በህገወጥ ሺያጭ ምክንያት መታገዱን ገልጸዋል ። ህገወጥነት ለማህበራዊ ህይወት ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ በህገወጥ ነጋዴዎች ላይ የተጀመረው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል ። የነዳጅ እረት እንዲፈጠር ማድረግ የህብረተሰቡን ኑሮ ችግር ውስጥ የሚጥል ህገወጥ ድርጊት በመሆኑ ህብረተሰቡ ለጸጥታ ሀይሉ ጥቆማ በመስጠት ሊተባበር እንደሚገባም ገልጸዋል። በተወሰኑ ጸጥታ ሀይል አካላት በኩል የሚስተዋል የስነምግባር ችግርም ሊሚታረም የሚገባ ነው ብለዋል። የመሐል ከተማ ክ/ከተማ

Ethiopian Premier League | Adama Kenema Vs Hawassa Kenema | አዳማ ከነማ ከ ሀዋ...

ከዱር እንስሳት እሰከ ውሃ አካላት የታደለ ስፍራ - ሎካ ዐባያ ፓርክ - ሲዳማ

የሲዳማ ክልል ውሃ ቢሮ እና ስራዎቹ

የሀብታሙ ገዛኸኝ ብቸኛ ግብ ሲዳማ ቡናን ባለ ድል አድርጓል

  በ14ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ቀን ውሎ በቀዳሚነት የተካሄደው የሲዳማ ቡና እና የአዲስ አበባ ከተማ ጨዋታ በሲዳማ ቡና 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል ። ሲዳማ ቡና በ14ኛው ሳምንት ከወልቂጤ ከተማ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ከነበረው ምርጥ 11 ሁለት ለውጥ ያደረጉ ሲሆን ግርማ በቀለ እና ብሩክ ሙሉጌታ ጊት ጋትኩትን እና ቴዎድሮስ ታፈሰን ተክተው የገቡ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ በኩል ደግሞ ሰበታ ከተማን በሰፊ ውጤት ሲረቱ በነበረው ቋሚ አሰላለፍ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ገብተዋል ። በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ሲዳማ ቡናዎች ኳሱን ይዘው በመጫወት ወደ ማጥቃቱ ሶስተኛ ዞን ለመግባት ጥረቶችን ያደረጉበት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ በኩል ደግሞ ኳሶችን በረጃጅም ወደ ፊት በመላክ የግብ አማራጮችን ለማግኘት የሞከሩበት ነበር ። በጨዋታው 9ኛ ደቂቃ ላይ እንዳለ ከበደ በረጅም የደረሰውን ኳስ በቀኝ መስመር በኩል ሆኖ ወደ ግብ ያሻገረውን ኳስ ሪችሞንድ ኦዶንጎ ለማግኘት ቢጥርም ኳሱ ላይ ለመድረስ ሳይችል ቀርቷል ። ከአንድ ደቂቃ በኋላም ሪችሞንድ በድጋሚ ከእንዳለ የደረሰውን ኳስ ጠንከር አድርጎ ባለመምታቱ በሲዳማ ቡና ተከላካዮች ተመልሶበታል ። በ24ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ በኩል ከቀኝ መስመር አቅጣጫ የተገኘውን የቅጣት ምት ሮቤል ግርማ ወደ ግብ ሞክሮት የግቡን አግዳሚ ለትሞ ወጥቷል ። ከውሀ እረፍት መልስ በተወሰነ መልኩ ሲዳማ ቡናዎች ጨዋታውን ተቆጣጥረው ለመጫወት ቢችለም ወደ አዲስ አበባ የግብ ክልል አልፈው ለመግባት ተቸግረው ነበር ። 34ኛው ደቂቃ ላይ ፍሬው ሰለሞን ከሳጥን ውጪ አክርሮ የመታው ኳስ ለጥቃት ወደ ውጪ የወጣ ሲሆን ከአራት ደቂቃዎች በኋላም ሳሙኤል አስፈሪ ኳስ ለማቀበል በሚሞክርበት ጊዜ ሀብታሙ ገዛኸኝ

ለመሆኑ በግብጽ እና ሳኡዲ አረቢያ አነሳሳሽነት በተመሰረተው የቀይ ባህር ፎረም ፤ የኢትዮጵያ አባልነት ተጠብቆ ነበር ወይ?

ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግስት ከቀይ ባህር ፎረም ውጭ መሆኑን በመቃዎም  ስሞታ ስያሰማ እየሰማን ነው። ለመሆኑ የቀይ ባህር ፎረም ምንድነው? እነማንን ያቀፌ ፎረም ነው? ከታች ያለው ዘገባ ዝርዝር ጉዳዩን ይዟል ፣ ያንቡት፤ New Red Sea alliance launched by Saudi Arabia, but excludes key players A new regional council involving eight countries in the Red Sea corridor was launched this week with Saudi Arabia at the helm as a way to tackle piracy, smuggling and other related issues. The council aims to enhance stability in the region, but regional rivalries and notable exclusions from the initiative remain a key sticking point.  “It seems for the moment that the piracy/maritime security angle is a good way to initiate cooperation between the countries of the region while staying outside of the political issues that may divide them,” said Camille Lons, research associate at the International Institute for Strategic Studies (IISS) Middle East in Bahrain. Foreign ministers from countries including Saudi Arabia, Sudan, Djibouti, Somalia, Eritrea, Egypt, Yemen, and J

ሰሚ ያጣው የሲዳማ ክልል ወጣት

የሲዳማ ክልል ወጣት ከተለያዩ የግልና የመንግስት ተቋማት ተመርቀው ቤት ከተቀመጡ ሶስት አመት ሆነ። ይህ ወጣት ሲዳማ ክልል እንዲሆን የአንበሳውን ድርሻ የተወጣ ነው። በአንጻሩ አሁን በስልጣን ላይ ያለው ቡድን ክልሉ እውን እንዳይሆን በስውርም ይሁን በህቡእ ሲሰራ የነበረ ቡድን ነው። ይህ ቡድን ከወንበሩ ሙቀት በላይ የወጣቱ ጩኽትና ሮሮ የማይሰማው ብኩን ስብስብ ነው። እስካሁን ባለን መረጃ በክልሉ ስራአጥ ወጣቶች በክልሉ ባሉ ከ30 ወረዳዎች እና 6 ከተማ አስተዳደር ያሉ ወጣቶች ድምጻቸውን በተለያየ ግዜ በተለያዩ መንገዶች ቢያሰሙም የደስታ ሌዳሞ መንግስት ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎታል። ይህ የወጣቶች እንቅስቃሴ ይበልጥ እየጨመረ በመምጣቱ ድምጹን ለማፈን ለተለያዩ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ማስጠንቀቅያ በመስጠቱ አንዳንድ ወረዳዎች ማሰር መጀመራቸው የዚሁ የማፈን አንዱ ሂደት ነው። ይህ ድርጊት ለወጣቱ ምላሽ መስጠት የማይችል አመራር መሆኑ ማሳያ ነው። በእርግጥ ጉዳዩ የመንግስት ብቻ ባይሆንም የሀገር ሽማግሌዎች የፖለቲካ ፖርቲዎች እንዲሁም የሲቪክ ተቋማትንም የሚመለከት ቢሆንም በሲዳማ ክልል ጠንካራ የሆነ እንዲህ ያሉ አደረጃጀቶች ባለመኖራቸው የወጣቱን ብሶት ሰሚ ለማጣቱ የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል። ሌላው እና ዋናው ደግም የክልሉን ህዝብ እንወክላለን ብለው በክልልም ይሁን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቀመጡ እንደከዚህ ቀደሙ ስርአት አጨብጭበው ከመውጣት በስተቀር የወጣቱን ጥያቄ አንድም ቀን ሲያሰሙ አይታይም ይልቁኑ ክልሉ ተወካይ ያለው እንኳ አይመስልም። እንዲህ ያሉና ሌሎች ለክልሉ ወጣት ድምጽ የሚሆኑ ባለመኖራቸው ወጣቱ በያለበት ሆኖ እንዲጮህ አስገድዶታል። ይልቁኑ በቀጣይ ትግል ምን ማድረግ እንዳለበትም እየወሰነ ነው። መንግስት የአጭር ግዜ እቅድ አውጥቶ የወጣቱን

የሲዳማ ክልል የባህል አዳራሽ ጉብኝት

የሲዳማ ክልል ስራ አጥ ተመራቂዎች በየወረዳዎቹ ሰላማዊ ስልፎችን ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ተሰምቷል

  የሲዳማ ክልል መንግስት በስራ ፈጠራ ላይ አስመዘገቡኩት የሚለው ውጤት እና በክልል ውስጥ ያለው እውኔታ ለየቅሉ መሆኑ የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው። የሲዳማ ክልል መንግስት አንድ ሰሞኑ በብሔራዊ ሚዲያዎች ላይ ወጥቶ አጥጋቢ የስራ ፈጠራ ስራ መስራቱን የሚገልጽ ሪፖርት ሲያሽጎዶጉድ፤ ክልል ባለው የስራ አፈጻጸም ለሌሎች ክልሎች ጭምር አርአያ የሆነ ሰራ መስራቱ በርካታዎቹ ስናገርሩ ተሰምተው ነበር። ነገርግን ፍዬል ወዲ ቅዥምዥም ወዲህ እንደሚባለው ተሰራ የተባለው የስራ ፈጠራ ስራ አንድም፤ ከዛሬ አራት እና አምስት አመታት ውስጥ በክልል የተተገበሩ ስራዎችን እና በነበሩት የስራ ፈጠራ እድሎች ተጠቃም የሆቡትን ወጣቶች ልክ በዚህ አመት አቅድ መሰረት ተጠቃሚ መሆን የቻሉ በማስመሰል የቲቪ ፕሮግራም ተሰርቶባቸዋል። ከዚህም ባለፈ በስራ ፈጠራ ፕሮጄክቱ ላይ ተሳትፎ ተጠቃሚ የሆነ እና ስራ የያዙ ወጣቶች ማንነት ላይም በርካታ ትችቶች እየቀረቡ ይገኛል። ይህ በዚህ እንዳለ፤ የክልሉ መንግስት በስራ ፈጠራ ከእቅድ በላይ ሰራው እያለ በሚመጻደቅበት በአሁኑ ጊዜ በየወረዳዎች ደረጃ የተደራጁ ከሶስት እና አራት አመታት በላይ ከዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ ሙያዎች ተመርቀው ስራ አጥተው የሚከራተቱ የክልሉ ተመራቂዎች በተደራጀ መልኩ ሰላማዊ ስልፎችን ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ተሰምቷል።  ለአብነት ያህል፤ ቀን 15-06-014 ዓ . ም ጉዳዩ፦ ሰላማዊ ሰልፍ እንድፈቀድልን እና የህግ ከለላ እንዲደረግልን ስለመጠየቅ ይሆናል። ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው እኛ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም እና ኮሌጆች ተመርቀን የወጣን ወጣቶች ባለፉት ሶስት / ሁለት አመታት በክልሉ የስራ እድል ሳይፈጠርልን መቆየታችን