በክልሉ በተለያዩ ኢንጂነሪንግ ሙያ ዘርፍና በአካውንታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምሮ የተመረቁ 432 ሥራ አጦችን በማህበር አደራጅተው በማሰልጠን ወደ ሥራ አሰማርተዋል
የተማረና የሰለጠነ የሰው ሀይል በመጠቀም ያለውን ውስን ሀብት ይዘው ወደ ሥራ በመግባት የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ችግር ለመፍታት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ገለጸ። በክልሉ በተለያዩ ኢንጂነሪንግ ሙያ ዘርፍና በአካውንታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምሮ የተመረቁ 432 ሥራ አጦችን በማህበር አደራጅተው በማሰልጠን ወደ ሥራ አሰማርተዋል። ============== ============ === በክልሉ ሥራ እድል ፈጠራ ፣ እንተሪፕራዞችና ማንፋክርግ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሠላሙ ቡላዶ በመድረኩ ተገንተው በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥራ ላጡ ዜጎች ሥራ እድል ለመፍጠር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በክልሉ 103 ሽህ 922 የሚሆን ዜጎች ልየታ የተደረጉ ሲሆን በገጠር መንገድ ሥራ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠልጥነው የተመረቁ ሥራ አጥ ወጣቶችን በመለየት ከአደራጁት 92 ማህበራት መካከል 72 የሚሆኑትን ሥልጠና በመስጠት ወደ ሥራ ማስገባት መቻላቸውን ገልጸዋል። በማህበር ተደራጅተው ሥልጠና ከወሰዱት 432 አሠልጣኞች መካከል 91 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውንም በማስያዝ። በክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ላታሞ በበኩላቸው በገጠር የሚገኙ የክልሉ ህዝብ ችግር ሆኖ የሚታየውን የመንገድ ዘርፍ ችግር ለመፍታት ቢሮው አቅደው እየሠራ እንደሆነ ተናግረው በበጀት አመቱ ይሰራል ብሎ ከአቀደው እቅድ መካከል 471.5 ኪሎሜትር የመንገድ ከፈታ ፣የጥርግያና የድልድይ ግንባታ ሥራዎች በመለየት ከሚመለክታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ለሥራ አጥ ወጣቶች ወደ ሥራ ለማሰማራት ቅድመ ዝግጂት ከተጠናቀቀ በኃላ በሥራ ላይ በሚያጋጥሟቸው ችግሮች ዙሪያ መፍተሔ ለማበጀት የሚያስ