Skip to main content

Posts

Showing posts from April, 2021

በክልሉ በተለያዩ ኢንጂነሪንግ ሙያ ዘርፍና በአካውንታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምሮ የተመረቁ 432 ሥራ አጦችን በማህበር አደራጅተው በማሰልጠን ወደ ሥራ አሰማርተዋል

የተማረና የሰለጠነ የሰው ሀይል በመጠቀም ያለውን ውስን ሀብት ይዘው ወደ ሥራ በመግባት የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ችግር ለመፍታት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ገለጸ። በክልሉ በተለያዩ ኢንጂነሪንግ ሙያ ዘርፍና በአካውንታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምሮ የተመረቁ 432 ሥራ አጦችን በማህበር አደራጅተው በማሰልጠን ወደ ሥራ አሰማርተዋል። ============== ============ === በክልሉ ሥራ እድል ፈጠራ ፣ እንተሪፕራዞችና ማንፋክርግ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሠላሙ ቡላዶ በመድረኩ ተገንተው በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥራ ላጡ ዜጎች ሥራ እድል ለመፍጠር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በክልሉ 103 ሽህ 922 የሚሆን ዜጎች ልየታ የተደረጉ ሲሆን በገጠር መንገድ ሥራ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠልጥነው የተመረቁ ሥራ አጥ ወጣቶችን በመለየት ከአደራጁት 92 ማህበራት መካከል 72 የሚሆኑትን ሥልጠና በመስጠት ወደ ሥራ ማስገባት መቻላቸውን ገልጸዋል።  በማህበር ተደራጅተው ሥልጠና ከወሰዱት 432 አሠልጣኞች መካከል 91 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውንም በማስያዝ። በክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ላታሞ በበኩላቸው በገጠር የሚገኙ የክልሉ ህዝብ ችግር ሆኖ የሚታየውን የመንገድ ዘርፍ ችግር ለመፍታት ቢሮው አቅደው እየሠራ እንደሆነ ተናግረው በበጀት አመቱ ይሰራል ብሎ ከአቀደው እቅድ መካከል 471.5 ኪሎሜትር የመንገድ ከፈታ ፣የጥርግያና የድልድይ ግንባታ ሥራዎች በመለየት ከሚመለክታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ለሥራ አጥ ወጣቶች ወደ ሥራ ለማሰማራት ቅድመ ዝግጂት ከተጠናቀቀ በኃላ በሥራ ላይ በሚያጋጥሟቸው ችግሮች ዙሪያ መፍተሔ ለማበጀት የሚያስ

የአረንጓዴ ልማትና ውበት ስራ በከተማዋ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ የሚገኝ ተግባር መሆኑ ተገለፀ

የአረንጓዴ ልማትና ውበት ስራ በከተማዋ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ የሚገኝ ተግባር መሆኑ ተገለፀ ============  የአረንጓዴ ልማትና ውበት ስራ በሃዋሳ ከተማ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ያለ ሰፊ ስራ እንደሆነ የሃዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊ እና የማስፈፀም አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ዝናሽ ሺማሎ ገለፁ፡፡ የሃዋሳ ከተማ በአረንጓዴ ልማትና ውበት ስራዎች ግንባር ቀደም ከሆኑ ከተሞች ተርታ የምትመደብና የአረንጓዴ ቦታዎች ላይ ልዩ ጥበቃ፣ እንክብካቤ እና በቂ ትኩረት በመስጠት የአረንጓዴ ሽፋንና ውበቷን በማስጠበቅ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ንጹህና ጤናማ እንድትሆን በርካታ ተግባራትን እያከናወነች የምትገኝ ውብ ከተማ መሆኗን በማስታወስ የአረንጓዴ ልማት ፅዳትና ውበት ስራ በከተማዋ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን ስራ መሆኑንና በዚህ ስራም የአመራሮች፣ የባለሙያዎች እና የነዋሪዎች ድርሻ ከፍተኛ የነበረ መሆኑን ኃላፊዋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡  ከበጀት ጋር በተያያዘም ከማዘጋጃቤት ገቢ የሚገኘው አብዛኛው ገቢ የሚመደበው ለደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ሲሆን የከተማዋን ፅዳትና ውበት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የተለያዩ የህብረተሰብ አደረጃጀቶችን በመጠቀም በየክፍለ-ከተማው በሳምንት አንድ ጊዜ ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው አካባቢያቸውን የማፅዳት ስራ ያከናውናሉ ያሉት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊዋ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የሃዋሳ ከተማ የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የእድገት ለውጦችን ማስተናገድና መሸከም የምትችል ውብ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ከተማ መሆን ችላለች፡፡  በቀጣይም ይህንን መልካም ስራ አጠናክረን እናስቀጥላለን በማለት ተናግረዋል፡፡ ሪፖርተር፡- ጌታቸው ኃይሉ ካሜራ ማን፡- ፈዬ ደሜ ----

የከተሞች ተቋማዊና መሰረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም (UIIDP) ሃዋሳ ከተማ አሁን ለደረሰችበት እድገትና ውበት ድርሻው የጎላ ነው ተባለ

ፕሮግራሙ ከተማዋ አሁን ለደረሰችበት እድገትና ውበት ድርሻው የጎላ መሆኑ ተጠቆመ   ====================== የከተሞች ተቋማዊና መሰረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮግራም (UIIDP) ሃዋሳ ከተማ አሁን ለደረሰችበት እድገትና ውበት ድርሻው የጎላ መሆኑን የሃዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊ እና የማስፈፀም አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ዝናሽ ሺማሎ ገለፁ፡፡ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በዓለም ባንክ ድጋፍ (UIIDP) ፕሮግራም ከታቀፉ ሶስት ከተሞች ውስጥ ሃዋሳ ከተማ የዚህ ፕሮግራም አንዷ ተጠቃሚ ነች፡፡  ይህ ፕሮግራም የከተማዋን የማስፈጸም አቅም መሠረት በማድረግ ከተማዋ ለነዋሪዎቿ በቂ የመሠረተ ልማት አገልግሎት ለማቅረብ እንዲሁም የኢንዱስትሪና የከተማ ልማት ፕሮግራሞችንና የከተሞች መልካም አሰተዳደር ፕሮግራሞችን በማስፋፋት፤ ዘላቂና ፈጣን ልማትን ለማረጋገጥና በተገቢው ሁኔታ ለማስፈጸም የሚያስችለን አቅም ገንብቶልናል ሲሉ ኃላፊዋ ወይዘሮ ዝናሽ ተናግረዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በከተማዋ ውስጥ ለሚከናወኑ የአረንጓዴ ልማት እና መሰረተ ልማት ስራዎች ትልቅ አቅምና ድጋፍ በመሆን ፕሮግራሙ ለሃዋሳ ከተማ እድገት ድርሻው የጎላ እንደሆነና በአሁኑ ሰዓትም በዚህ ፕሮጀክት እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በመልካም ሁኔታና በጥንቃቄ እተመሩ ነው ሲሉ ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡ ኃላፊዋ አያይዘውም በፕሮግራሙ ለተለያዩ ተቋማት አቅም የመገንባት ተግባርን ጎን ለጎን አጠናክረን ያስቀጠልንበትና ፕሮግራሙ የታለመለትን ዓላማ ከግብ እንዲመታና ሃዋሳ ከተማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭና ተወዳዳሪ እንድትሆን ከሚመለከታቸው አካላትና ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ ከተማዋ በፕሮግራሙ ከታቀፈችበት ጊዜ ጀምሮም በከተማዋ ይስተዋሉ የነበሩ የመሰረ

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በወንዶችና በሴቶች ሀገርአቀፍ ውድድር በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነ

የሐዋሳ ከተማ በቅርጫት ኳስ ሻምፒዮን ሆነ!! በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በወንዶችና በሴቶች ሀገርአቀፍ ውድድር በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነ። በትናንትናው ዕለት በተጠናቀቀው ሀገር አቀፍ የቅርጫት ኳስ ውድድር ከተማው በሁለቱም ፆታ ማሸነፉን ተከትሎ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ተጫዋቾቹን በአካል ተገኝተው እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን በማለት የደስታው ተካፋይ ሆነዋል።  ክቡር ም/ከንቲባው አክለውም ይህ ውጤት በከተማው ውስጥ ያለውን ዕምቅ አቅም ያሳየ እና ለህዝቡም መነቃቃትን የሚፈጥር ሲሆን አሁን ያሉ የስፖርት ሜዳዎች ችግሮችን በተመለከተ ከተማ አስተዳደሩ በርካታ ጥረቶችን እያደረገ ነው ይህ ውጤት ደግሞ ይበልጥ ጥያቄዎቹ እንዲፈቱ ጫና የሚፈጥር ስለሆነ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራበታል ብለዋል። ወ/ሮ ደርጊቱ ጫላ የከተማው ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ በሁለቱም ፆታ በማሸነፋቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ስፖርት አንዱ እና ዋነኛው የቱሪዝም ዘርፍ በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ሲሆን የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን ለአፍሪካ ውድድር በሚመጥን መልኩ ከተማ አስተዳደሩ ይሰራል ብለዋል። የከተማው የሴቶች ቅርጫት ኳስ አሰልጣን ወጣት አስተዋይ አበበ በውጤቱ መደሰታቸውን አንስተው ከስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ከተቀረፉ ከዚህ የተሻለ ደረጃ መድረስ የሚችል አቅም አለን ብለዋል። የሐ/ከ/አስ/መ/ኮ/ጉ/መምሪያ    ሚያዚያ 20/2013ዓ.ም       ሐዋሳ

የሲዳማ የአየር ጠባይ ለአፕል ምርት አመቺ ነው

የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ተመራማሪዎች አፕል ምርት በተመለከተ የሲዳማ የአየር ጠባይ አመቺ እንደሆነ ይናገራሉ። ተመራማሪዎች እንደምሉት "የአፕልን ምርት የሚወስነው የቅዝቃዜ መጠን ነው። ኢትዮጵያ አፍሪቃ ውስጥ ካሉ አገራት በተለይ ተለዋጭ የአየር ጠባይ ስላላት እጅግም ቀዝቃዛ እጅግም ሞቃት ያልሆነ አማካኝ የሙቀት መጠን ይገኝባታል። ስለዚህ ደጋማው አካባቢ በአጠቃላይ ለበርካታ የአፕል ዝርያዎች አመቺ ሁኔታን ይፈጥራል። በአንድ በኩል የአየር ጠባዩ አመቺ ነው። ሁለተኛ በደጋማ አካባቢ የሚኖረው አርሶ አደር የምርት አይነቱ ውስን ስለሆነ ቋሚ የሆነ አትክልት እና ፍራፍሬ ከሌላው ሰብል ጋር አጣምሮ ቢያመርት በጣም ጠቃሚ እንደሆነ ይመከራል።" "አፕል የደጋ ፍራፍሬ ነው። በተለምዶ ደጋማ ወይም ቀዝቃዛማ በምንለው የአየር ንብረት ውስጥ ተተክሎ ፍሬ መስጠት የሚችል ነው። ይኸ ዛፍ የራሱ የሆነ የስር ክፍል አለው። የራሱ የሆነ ፍሬ ሰጪ ክፍል አለው። እነዚህን ሁለቱን ክፍሎች በከተባ ወይም በማዳቀል ዘዴ በማገናኘት ችግኙ ይዘጋጃል። ለተከላ የሚደርሰው ችግኝ 3 አመት ይወስዳል። በዚህ ደረጃ የተዘጋጀው የአፕል ችግኝ በአግባቡ ከተተከለ እና አስፈላጊው እንክብካቤ ከተደረገለት በደንብ ፍሬ ሊሰጥ ይችላል።" ከባህር ጠለል በላይ ከ1, 800 እስከ 3, 000 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኙ ደጋማ አካባቢዎች አፕል ለማምረት ምቹ ናቸው። መነሻው ከወደ አውሮጳ እና የእስያ አገራት ነው። አንድ የአፕል ዛፍ እንደ እፍጋቱ መጠን* (density) ከ40-200 ኪ.ግ. ምርት ይሰጣል። የአፕል ገበሬዎች ይኸንን የፍራፍሬ ዝርያ ለኑሮ መደጎሚያ ፤ ለንጥረ-ምግብ ይዘቱ (ቫይታሚን ሲ) እንዲሁም የአፈር መከላትን ለመከላከል ይተክሉታል።    &quo

Tayxe Fichee-cambalaalla Dotteessa 29-30 hossannota Sidaamu budu geerri xawissino

Odoo| Fichee-cambalaalla ===================== Tayxe Fichee-cambalaalla Dotteessa 29-30 hossannota Sidaamu budu geerri xawissino. Malu songora leellinohu Ayirradu Kalaa Bayyani Ba'raasihu Sidaamu Dagoomu Qoqqowi Mootimma 2ki Pirezidaantichinna Rosu Biiro Sooreessi gobbate geerrira Fichee Sidaamaho bayra ayyaana ikkitinotanna Fichee-cambalaalla baadinnino kalaqe afamishsha uytino ayyaana ikkitinota xawisino. Qoleno, tayxe Fichee-cambalaalla ayirrisate malira gamba yiino geerrira baadi odoo roorinni COVID-19 iillishanni noo gawajjo eersino. Ledeno, Sidaamu Dagoomu Qoqqowu Mootimma Woga, Turizimenna Ispoortete Biiro Sooreessi Kalaa Jaggo Aganyohu, Fichee-cambalaalla Sidaamu woga helliicho ikkitinota xawise, tenne woga amaxxate, egensiisi'ratenna ilamate sayisi'rate Sidaamu Dagoomu Qoqqowu Mootimma kalaqi'rate qiniiti majjaha ikkinota hawaqisino. Niri Fichee-cambalaalla COVID-19 fayya korkaatinni geerchu mannu mine minesi ayirrise sa"anno gede sokka saysi

Fayinansete Biiro Inisipekishiinenna giddo odiite afantinno xe'ne aana

Sidaamu Dagoomu Qoqqowi Mootimma Fayinansete Biiro Inisipekishiinenna giddo odiite afantinno xe'ne aana hasaanbe aantete loossara faasho worranni hasaawu bare hawaasi quchumira harissanni afantanno. Sidaamu Dagoomu Qoqqowi Mootimma Fayinaansete Biiro Soreessi Kalaa Ararso Gerremewuhu Bushshu Madaabbarinna babbaxinno korikaatinni xe'ne leeltinno Woxe konni dirinni qolsiisate amandoonni mixo giddo 9aganinni qolsinsoonnihu aje leellinota xawise tenne bare gedenssaanni murcci'ne loosa hasiissannota xawise Ayiirrado barru wosincho hasaawu bare fananno gede koyiisinno. Ayiirradu barru Wosinchi kalaa Asufi Goneessohu Sidaamu Qoqqowi Jireenyu Paarte Bo/mini Riyoote Alametenna Poletiku handaari soreessi hasaawu bare fani yannara mitte gobbara xinttu latishsha abbate hasiisannohu qajeela mannu wolqanna woxu woliqa ikkitinnota kule noonketa shiima jiro amandanninna gashshinanni amanyooti aana soorro abba hasiissannota coyii're xaa geeshsha odiitetenni afaminno woxe see

ወጣቷ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ

የመራሒት ድጋፍ በሀዋሳ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች «መራሒት» በሚል ባቋቋሙት ክበብ አማካኘነት የገንዘብ አቅም የሌላቸው ተማሪዎችን እየደገፉ ይገኛሉ። ከክበቡ አስተባባሪዎች አንዷ የሁለተኛ ዓመት የሕግ ተማሪ ተቋም አማረ አንደምትለው ክበቡ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተማሪዎች የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ድጋፍ ያደርጋል። የስነ ልቦና ማጠናከሪያ ስልጠናዎችንም በመስጠት ላይ ነው። የመራሂት ድጋፍ በሐዋሳ

በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችል ስልጠና ተሰጣቸው

  ወጣቶች ስራ ፈጣሪ ሊሆኑ ይገባል። የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ። በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችል ስልጠና ተሰጣቸው። ወጣቶቹ ከስምንቱም ክ/ከተማ የተውጣጡና በ100 ማህበር የተደራጁ ሲሆኑ ከ500 በላይ የሆኑ የድግሪ ምሩቃን ናቸው። በተለያየ የሙያ ዘርፍ የሰለጠኑ ወጣቶች እንደመሆናቸው ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን የገለጹት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/መምሪያ ሀላፊና የስራ እድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ዘርፍ ሀላፊ አቶ አሻግሬ አበበ ናቸው። አቶ አሻግሬ ወጣቶች የስራ ፈጠራ ምንነትን ተገንዝበው፣ ስራ ፈጣሪ መሆን እንደሚችሉ አምነው እና በአግባቡ የተዘጋጀ እቅድ ይዘው ወደስራ ከገቡ ውጤታማነታቸው አያጠራጥርም ብለዋል። በከተማ አሰተዳደሩ ድጋፍ እየተሰሩ ያሉ ሼዶች የወጣቶቹን የቤት ኪራይ ወጪ የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ የተገነቡት ለስራ አመቺ በሆነ ቦታና ደረጃውን በጠበቀ ጥራት መሆኑን ነው አቶ አሻግሬ ያከሉት። ወጣቱ ራዕይ ኖሮት፣ ስንፍናን አስወግዶና ጊዜውን በስራ ማሳለፍ ከቻለ እንደሀገርም ድህነትን ለመቀነስ መፍትሄ እንደሚሆን ነው አቶ አሻግሬ የገለጹት። በስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶች በበኩላቸው ይህ ስልጠና የተሰጠን ስራ ከመጀመራችን በፊት መሆኑ እራሳችንን በተለያየ ነገር እንድናሳምንና ዝግጁ እንድንሆን አስችሎናል ብለዋል። ለወጣቶቹ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሰጠው ኢንተርኘርነርሺኘ ልማት ማህበር (EDC) ኢትዬጵያ ነው። ስልጠናው በውስጣችን የነበረ ስጋትንም ያስወገደ ነው ሲሉ ሰልጣኞቹ ገልጸዋል። ከሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ ልማት መምሪያ ጋር በመተባበር ለወጣቶቹ የግንዛቤ

Dire Dawa gets crucial win over Sidama Coffee

  Dire Dawa earned a morale-boosting 1-0 win over Sidama Coffee at the Dire Dawa International Stadium with Muhedin Musa scoring from the penalty spot on the stroke of halftime. Bereket Samuel hit a long-range shot from a freekick for Dire Dawa in the 14th minute, but Fikre Wedesa dealt with it well. This was followed by another long-range shot from Awot Gebremikael, who rattled the crossbar. Dire Dawa's pressure paid off in the 44th minute when Sunday Mutuku, Sidama's defender, was adjudged to have handled the ball in the penalty area, though he was moving his hands behind him as Surafel Getachew tried to get past. Muhidin stepped up and sent Wedesa the wrong way to make it 1-0 just before halftime. The second half began with Dire Dawa still on top and Getachew almost made it 2-0 with a freekick which Wedesa fumbled but recovered in time to prevent the goal. Sidama then created two good chances for their star striker, Okiki Afolabi, who in the 79th and 82nd minute rattled the

Urban Expansion in Ethiopia from 1987 to 2017: Characteristics, Spatial Patterns, and Driving Forces

  Abstract Rapid urban growth in major cities of a country poses challenges for sustainable development. Particularly in Africa, the process of rapid urbanization is little understood and research is mostly limited to single cities. Thus, this study provides a comprehensive comparative analysis of the growth and spatial patterns of urban development in the three major cities of Ethiopia (Addis Ababa, Adama, and Hawassa) from 1987 to 2017. Also, the applicability of diffusion and coalescence theory on the evolution of these cities has been tested. Remote sensing and GIS technologies were combined with spatial metrics and morphological analysis was employed to undertake this study. The result revealed that all the studied cities experienced accelerated growth in the urbanized areas, but the cities with a larger initial urbanized size were associated with lower expansion rates. Differences in extent and direction of expansion in each city were mostly related to physical features, urban ma

የሲዳማ ክልል ለሰላም መረጋገጥ የሚያደርገው ጥረት በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ኮሚቴው ገለጸ

  የሲዳማ ክልል ለሰላም መረጋገጥ የሚያደርገው ጥረት በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ኮሚቴው ገለጸ (ዜና ፓርላማ) ሚያዚያ 7/2013 ዓ.ም፤ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከኦሮሚያ እና ከደቡብ ክልሎች ጋር ያለውን ሰላማዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያደርገው ጥረት በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን ገልጿል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ይህን የገለጸው ሰሞኑን መክልሉ ባደረገው የመስክ ምልከታ ወቅት ሲሆን ክልሉ የኅብረተሰቡን ሰላም እና ደህንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ልማታዊ እንቅስቃሴዎች በጸረ-ሰላም ኃይሎች እንዳይደናቀፉ ለማድረግ ከአጎራባች ክልሎች ጋር እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብሏል፡፡ የቋሚ ኮሚቴ አባል የተከበሩ አቶ ቡንጡቃ ዋሬ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ የክልሉን ልማት ከማረጋገጥ እንዲሁም ዜጎች በብሔራቸውና በዕምነታቸው ምክንያት ሳይሸማቀቁ ከየትኛውም የፀጥታ ስጋት ነጻ ሆነው በክልሉ ተንቀሳቅሰው ሀብት የማፍራት ህገ-መንግስታዊ መብታቸው እንዲከበር ከአጎራባች ክልሎች ጋር እየሰራ ያለው የተቀናጀ ሥራ ለሌሎችም ተሞክሮ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። የተከበሩ አቶ ሻምበል ነጋሳ በበኩላቸው ሀገሪቱ በአሁኑ ስዓት የጀመረችውን የለውጥ እንቅስቃሴ ከግብ እንዳይደርስ ለማደናቀፍ፣ ዜጎች በአብሮነትና በአንድነት መኖር የማይዋጥላቸውና ህልውናቸው ዜጎችን በመረበሽ፣ በመግደል እና በማፈናቀል ላይ የተመሰረተ ጸረ-ሰላም ቡድኖችን ከመከላከል እና እርምጃዎችን ቀድሞ ከመውሰድ አንፃር እንዲሁም በመንግሥት መዋቅር ስር የተሰገሰጉ ኪራይ ሰብሳቢዎችን ክልሉ ወደ ህግ ማቅረቡ የሚያበረታታ ነው ብለዋል፡፡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሰላምና የጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ

አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰው የኮሮና ስርጭት – በሲዳማ

  በሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ አንቱታን ያተረፉት አቶ ተፈራ ዊላ፤ በብዙዎች ዘንድ የሚታወቁት “ለተቸገረ ሁሉ ደራሽ” በመሆናቸው ነው። ይህ የበጎ አድራጎት ተግባራቸው በሀዋሳ ብቻ ሳይሆን በብዙ የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ወዳጅ እንዳፈራላቸው የቅርብ ሰዎቻቸው ይናገራሉ። ተጨዋች እና በቀላሉ ተግባቢ መሆናቸውም ለዕውቅናቸው እንዲናኝ ምክንያት ሆኗል። “የሆስፒታልን ደጃፍ እምብዛም ረግጠው አያውቁም” የሚባልላቸው አቶ ተፈራ፤ ከሰሞኑ ወደ ህክምና ተቋም ጎራ እንዲሉ ያደረጋቸው የህመም ስሜት ገጥሟቸው ነበር። የህመሙ ስሜት በመጀመሪያ “ጉንፋን ነው” በሚል ችላ ብለውት የነበረ ቢሆንም፤ ከቀናትም በኋላ አለመጥፋቱ ግን በቅርብ ሰዎቻቸው ጥርጣሬ ማስከተሉ ለነገሩ ትኩረት እንዲሰጡ አስገድዷቸዋል። የአቶ ተፈራ ወዳጆች ከህመማቸው ምልክት ተነስተው የተጠራጠሩት “ምናልባትም በሽታው ኮሮና ሳይሆን አይቀርም” የሚል ነበር።   ቅዳሜ መጋቢት 18፤ 2013 ወደ ሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል የሄዱት አቶ ተፈራ፤ ኮሮና ይኖርባቸው እንደው ለማወቅ ናሙና ከሰጡ በኋላ ውጤታቸው እስኪታወቅ በህክምና ተቋም እንዲቆዩ ይደረጋሉ። ከሁለት ቀናት በኋላ የመጣው የምርመራ ውጤት ታዲያ የቅርብ ሰዎቻቸውን ጥርጣሬ ያረጋገጠ ሆነ። ውጤቱ ከጠበቁት በተቃራኒ የሆነባቸው አቶ ተፈራ፤ የጤና ባለሙያዎች የነገሯቸውን ለማመንም ሆነ ለመቀበል ተችግረው እንደነበር የሚያውቋቸው ይናገራሉ። በኮሮና ቫይረስ እንደተጠቁ ማወቃቸው የፈጠረባቸው ጭንቀት የጤንነታቸው ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሽቆለቆል ሰበብ መሆኑንም ይገልጻሉ።  የአቶ ተፈራ ሁኔታ ያሳሰባቸው የህክምና ባለሙያዎች፤ የአተነፋፈስ ስርዓት እንዲስተካከል የሚያግዘውን ኦክስጅን ሊያጠልቁላቸው ሙከራ ቢያደርጉም፤  ኸህመምተኛው የገጠማቸው ብርቱ እምቢተኝነት ግን ያሰቡትን ማ

አዲሱን ክልል መፈተን የጀመሩት የወሰን እና አስተዳደር ጥያቄዎች

የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ስልጣኑን ከተረከበ ከሶስት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ ተደጋግመው ከሚታዩ ፖለቲካዊ ትኩሳቶች መካከል፤ የክልሎች ወሰንና የማንነት ጉዳዮች፣ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ እና “በዚህኛውም አሊያም በዚያኛው ክልል መተዳደር እንፈልጋለን” የሚሉ ተደጋጋሚ ድምጾች ይገኙበታል። እኒህን መሰል ጥያቄዎች ከተቋቋመ 10 ወራትን ብቻ ወዳስቆጠረው ወደ አዲሱ የሲዳማ ክልልም መሻገር ጀምረዋል።  ክልሉ በያዝነው በመጋቢት ወር ብቻ በሶስት ቦታዎች ላይ ከወሰን ጉዳዮች ጋር በተገናኘ ችግሮች ገጥመውታል። ሁለቱ ጉዳዮች የተያያዙት በኦሮሚያ ክልል ከሚገኘው ምዕራብ አርሲ ዞን ሲሆን አንዱ ደግሞ በደቡብ ክልል ከሚገኘው የወላይታ ዞን ጋር ነው። ከሁነቶቹ ሁሉ ከበድ ያለውና በጊዜ ረገድም ቀረብ ያለው፤ ባለፈው ሳምንት አርብ መጋቢት 24፤ 2013 በክልሉ ስር በምትገኘው ወንዶ ገነት ወረዳ የተከሰተው ነው።  በዕለቱ በወረዳው ስር ካሉ ቀበሌዎች አንዷ በሆነቸው ኤዶ ያሉ የታጠቁ ኃይሎች የመከላከያ ሰራዊት ላይ ተኩስ እስከ መክፈት ድረስ የተጓዘ ጥቃት መፈጸማቸውን የክልሉ ባለስልጣናት ይናገራሉ። የመከላከያ ሰራዊቱ በአካባቢው የተሰማራው ከሁለት ዓመት በፊት በስፍራው የተፈጠረውን ግጭት ለማረጋጋት በሚል ሲሆን እስካለፈው ሳምንትም በኤዶ ቀበሌ ቆይቷል። ኤዶ ቀበሌ በኦሮሚያ ምዕራብ አርሲ ዞን እና በሲዳማ ክልል ድንበር ላይ ከሚገኙ 13 ቀበሌዎች አንዱ ነው። የጉጂ ማህበረሰብ ተወላጆች የሚኖሩባቸው እነዚህ ቀበሌዎች በምዕራብ አርሲ አሊያም በሲዳማ ስር ይተዳደሩ የሚለው ጉዳይ ሲያወዛግብ ቆይቶ ምላሽ ያገኘው በ2001 ዓ.ም. ነበር። በወቅቱ በቀበሌዎቹ ላይ በተካሄደ (ህዝበ ውሳኔ) ኤዶን ጨምሮ ዘጠኝ ቀበሌዎች በሲዳማ ስር እንዲሆኑ ሲወሰን ቀሪዎቹ አራት ቀበሌዎች በምዕራ

አቶ ደመቀ መኮንን በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከተመራው የአውሮፓ ህብረት ልዑክ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የአውሮፓ ህብረት ልዑክ መሪ ፔካ ሀቪስቶ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸው ትግራይ ክልል የሚሰያስፈልገውን ሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት የኢትዮጵያ መንግስት ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሚሸፍን መሆኑን ጠቅሰው እስካሁን ለ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታ እያቀረበ መሆኑን አቶ ደመቀ አስታውሰዋል። በሌላ በኩል በክልሉ ቀደም ሲል ሲተገበር የነበረው የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም የተጀመረ መሆኑን የገለፁጽት አቶ ደመቀ ይህም በክልሉ ሁኔታዎች ወደ መደበኛ ሁኔታ እየተመለሱ ስለመሆኑ አመላካች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ምርመራ ከማደረግ አንጻር የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ቀደም ሲል በማይካድራ እንዲሁም በመቀጠልም በአክሱም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ምርመራ በማድረግ ያቀረበውን ሪፖርት አስታውሰው በመንግስት በኩል በገለልተኛ አካላት አማካይነት ምርመራ እንዲደረግ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በሰብዓዊ መብት ጥሰት የተሳተፉ አካላትን ለህግ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት አቶ ደመቀ አረጋግጠዋል። ፔካ ሀቪስቶ በበኩላቸው ከሁለት ወራት በፊት በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጋቸውን አስታውሰው፣ ከዚያ በኋላ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ተደራሽነትና የሚዲያ አካላት በክል በመገኘት እንዲዘግቡ ከማድረግ አንጻር በመንግስት የተከናወኑ ተግባራት በአዎንታዊነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። በክልሉ ያደረጉት ጉብኝትም ይህንን የሚያረጋግጥ መሆኑን ያነሡ ሲሆን ግጭት ያለባቸው የተወሰኑ አካባቢዎች እርዳታ የሚያስፈለጋቸው ዜጎች ተገቢው እርዳታ እንዲደርሳ

በአገራችን እየታየ ላለው መፍትሄ ላጣነው የብሄር ተኮር ግጭት መቋጫ እንድኖረው፤ የኮሎምቢያ የብሄሮች ጥምረት ለሰላም አካሄድ በምሳሌነት ወስደን መተገበር ለነገ የሚባል አይደለም

Colombia PGO - Inter-Ethnic Alliance for Peace The Inter-Ethnic Alliance for Peace Activity strengthens Indigenous and Afro-descendant communities’ advocacy, self-governance, organizational and leadership capacities. The activity also improves food security, supports income generation activities, and promotes regional peacebuilding in alignment with the Peace Accord’s Ethnic Chapter. The activity is implemented by two of the most relevant Indigenous and Afro-descendant organizations in Colombia, the National Association of Displaced Afro-Colombians (AFRODES) and the National Indigenous Organization of Colombia (ONIC). The Inter-Ethnic Alliance for Peace Activity is implemented in Cesar, Chocó and La Guajira, and it runs from January 2021 to December 2023. COMPONENTS ENHANCING AUTONOMY AND SELF-GOVERNANCE The Inter-Ethnic Alliance for Peace Activity strengthens Indigenous and Afro-descendant community organizations’ leadership capacities and self-government structures. The activity supp

6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተዓማኒ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በህዝቦች ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን መራጩ ህብረተሰብ ንቁ ተሳ...

በከተማ ዳርቻ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ ተባለ

በርግጥ ሐዌላ- ቱላ ክፍለ ከተማ፤ የሐዋሳ ከተማ አንድ አካል መሆኑ፤ በሬዳና - ደኢህዴን ዘመን፣ በከተማችን የሲዳማን ተወላጅ ነዋሪ ቁጥር ከማሳደጉ እና የበላይነት እንዲኖረው፤ ብሎም "የሜትሮፖሊቲያን ከተማችን" የሚለውን የደኢህዴን ማንፌስቶን ከማክሽፍ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ነገር ግን ምንም እንኳን ለሲዳማ ፖለቲካ ወሳኝ ብሆንም፤ እንዝላል ፖለቲከኞች የክፍለ ከተማውን ነዋሪ አርሶ አደሮችን በማፈናቀል፤ መሬቱን ስቸበችቡ ቆይተዋል። የሐዋሳ ከተማ ክፍለ ከተማ ሆነው ውሃ፣ መንገድ እና መብራት ሳይኖረው ያን ሁሉ ዘመን መዝለቁ፤ ለዚህ ማሳያ ነው። ሲዳማውያን፤ የሐዌላ- ቱላ ክፍለ ከተማን ውለታ እንርሳ!!

ኮሚቴው በሀገር ውስጥ ህፃናት እንክብካቤ ላይ ለሚሰሩ ተቋማት ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ጠቆመ

በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙ ህጻናት በጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ተጥለው የተገኙ እንደሆነና አንዳንዶቹ ደግሞ የአካል ጉዳተኛ መሆናቸውን አስረድተው ስራው ከተጀመረ 15 ዓመት ቢሆንም ቦታ እንዲሰጣቸው በየጊዜው ቢጠይቁም ትኩረት እንዳልተሰጣቸውና እስካሁን በችግር ላይ መሆናቸውን የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ አርጋው አየለ ተናግረዋል፡፡ እንግዲህ የሲዳማ ክልል ለዚህ አይነት መልካም ተግባር እና ሰብአዊነት፤ መልካም ምሳሌ ለሆኑ ግለሰቦች እና ተቋማት፤ መሬትን እና የመሳሰሉ ድጋፎችን ማድረግ ይጠበቅበታል የሚል እምነት አለኝ።   ኮሚቴው በሀገር ውስጥ ህፃናት እንክብካቤ ላይ ለሚሰሩ ተቋማት ተገቢው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ጠቆመ (ዜና ፓርላማ)፣ መጋቢት 29/2013 ዓ.ም.፤ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማ የሚገኘውን አብየኔዘር ሰፖርቲንግ ዴቨሎፐመንት አሶሴሽን ህጻናት ማሳደጊያ ጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱም የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ አርጋው አየለ ድርጅቱ በ1998 ዓ.ም እንደተመሰረተና በወር ለኪራይ 80 ሽህ ብር በመክፈል ህጻናትን በማሳደግ ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙ ህጻናት በጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ተጥለው የተገኙ እንደሆነና አንዳንዶቹ ደግሞ የአካል ጉዳተኛ መሆናቸውን አስረድተው ስራው ከተጀመረ 15 ዓመት ቢሆንም ቦታ እንዲሰጣቸው በየጊዜው ቢጠይቁም ትኩረት እንዳልተሰጣቸውና እስካሁን በችግር ላይ መሆናቸውን የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ በጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ላይ ከፍተኛ ስራ እንደሰራና ትምህርት ቤት ምገባም ላለፉት 5 ዓመታት በተከታታይ ለ51 ትምህርት ቤቶች 31‚700 ህጻናትን ምገባ ማድረጉንም አብራርተዋል፡፡ ይሁን እንጂ

የሐዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ መሪ ፕላን ትግበራ በይፋ ተጀመረ

  የሐዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ መሪ ፕላን ትግበራ በይፋ ተጀመረ። ትግበራው በዛሬው ዕለት በይፋ የተጀመረው የሐዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ መሪ ፕላን ኢኮኖሚያዊ, ማህበራዊና መዋቅራዊ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ገለፀዋል። የጥናትና የዝግጅት ስራው የተጠናቀቀው መዋቅራዊ ፕላኑ የትግበራ ምዕራፍ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ፣ በኢትዮጽያ የብሪቲሽ ኢምባሲ ተወካይ ጆን ፖል ፋኒንግ፣ በኢትዮጽያ የጃፓን ኢምባሲ ተወካይ ኢዳ ቶሺኦ፣ ወ/ሮ ሀረገወይን በቀለ በኢትዮጽያ የዩኤን ሀቢታት ፕሮግራም ማናጀር እንዲሁም የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሀቢታት ፕሮጀክት በኢትዮጽያ አማካኝነት ሲጠናና ሲዘጋጅ የቆየው ከ2020-2030 ዓም የሚተገበረው የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር መዋቅራዊ መሪ ፕላን በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር እየተገመገመ የጥናትና የዝግጅት ምዕራፉ በስኬት መጠናቀቁንም ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ገልፀዋል። ቀጣይነት ያለው ሁለንተናዊ ዕድገትና ልማት በማስመዝገብ ከተማዋን ለኑሮ፣ ለቱሪዝም፣ ለኢንቨስትመንትና ለኢንዲስትሪ በዘላቂነት ምቹ የማድረግ ራዕይን ለማሳካት መሪ ፕላኑ ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረውም ክቡር ከንቲባው አመላክተዋል። የሐዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ መሪ ፕላን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና መዋቅራዊ ችግሮችን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ በይፋ ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ወቅት ገልፀዋል። 49 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ገንዘብ ተሰርቶ የተጠናቀቀው የሐዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ መሪ ፕላን በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ በዩኤን ሀ

Hawassa Kenema are in ninth spot and could prove formidable and dent Coffee's charge.

By Emeka Enyadike 06 April 2021 | 16:31 Abubakher Nasri of Ethiopia Coffee © SuperSport.com The Betking Ethiopia Premier League returns on Thursday at the Dire Dawa Stadium in Dire Dawa, a city famous for hosting matches for Afcon 76 as St George and especially Ethiopia Coffee look to challenge Fasil Kenema’s runaway lead at the top of the log. With action set to resume after a two-week break there will be some players who might feel the effects of international duty. In addition, a series of game postponements are sure to to further break the rhythm for some teams as they try to find their range. One significant change from the games will be the late kick-offs because of the temperature. This will be the first time this season when there will not be a morning kickoff. St George v Sebeta Kenema - Wednesday, 7 April St George have fallen below their usually high standards and have parted ways with coach Mahir Davids, so this is an opportunity to reset their season as they

የኮቪድ 19 ክትባትን በመከተብና የመከላከያ መንገዶችን በመተግበር ኮቪድ 19ኝን በጋራ እንከላከል!

HAWASSA UNIVERSITY Documentary

Ethiopia: ሰበር መረጃ

የተቋረጠው የሐዋሳ ስቴዲዬም ግንባታ እንዲቀጥል ኮሚቴው አሳሰበ

የተቋረጠው የሐዋሳ ስቴዲዬም ግንባታ እንዲቀጥል ኮሚቴው አሳሰበ  (ዜና ፓርላማ)፤ መጋቢት 2013 ዓ.ም.፣ ሐዋሳ፤ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የተቋረጠው የሐዋሳ ስቴዲዬም ግንባታ እንዲቀጥል አሳሰበ፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው፤ ሰሞኑን በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሐዋሳ ከተማ የመስክ ምልከታ በአካሄደበት ወቅት ነው፡፡ የግንባታውን አሁናዊ ይዞታ የገመገመው የስቴዲዬሙ ግንባታ የቴክኒክ ኮሚቴ፤ ከዐቢይ ኮሚቴ በሚሰጠው አቅጣጫ ተመሥርቶ ወደ ግንባታ ለመግባት የሚያስችለውን ሁኔታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንዲያመቻችም የቋሚ ኮሚቴው ቡድን ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ሞሚና መሐመድ አመላክተዋል፡፡   የሐዋሳ ስቴዲዬም ግንባታ የመጀመሪያ ምዕራፍ የተጠናቀቀ ቢሆንም፤ ለአደጋ ተጋልጦ አገልግሎት ሳይሰጥ መቀመጡ ተገቢ ባለመሆኑ ለችግሩ መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባ ቋሚ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡ በተጨማሪም ከስፖርቱ ዘርፍ ጋር ተያይዞ ጤናማ እና ብቁ ዜጎችን ለማፋራት የስፖርት ማዘዉተሪያዎች ትልቅ ሚና ስላላቸዉ በቂ ትኩረት ለዘርፉ እንዲቸርም ኮሚቴው አያይዞ አስገንዝቧል፡፡ የሐዋሳ ዓለም-አቀፍ ስቴዲዬም ሳትኮን ከተሰኘ ሀገር-በቀል የግንባታ የግል ኩባኒያ ጋር በተደረገው ስምምነት መሠረት በ7 መቶ ሚሊዬን ብር የተገነባ ሲሆን፤ የመጀመሪያ የግንባታ ምዕራፉን በውሉ መሠረት ማጠናቀቁን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ እናም የሲዳማ ክልል የባሕል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ፤ ይህ ግልጽ ባለቤት የሌለው እና ምንም ዓይነት ርክክብ የአልተደረገለት ስቴዲዬም የፌዴራል መንግስትን ምላሽ እንደሚፈልግ ጠቁመዋል፡፡  የሲዳማ ክልል ዕምቅ የባህል እና የቱሪዝም ሀብት ባለቤት ከመሆኑ ጋር ተያ