Skip to main content

Posts

Showing posts from February, 2021

በ13 ቢሊዮን ብር በመካሄድ ላይ ያለው የሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ለምን ለአመታት ተጓተተ

በ13 ቢሊዮን ብር በመካሄድ ላይ ያለው የሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ለምን ለአመታት ተጓተተ  በ13 ቢሊዮን ብር በመካሄድ ላይ ያለው የሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ላለፉት በርካታ አመታት ግንባታው ከምገባው በላይ በመጓተት ላይ በመሆኑ፤ ጉዳዩ የሚመለከተው የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልል መንግስታት፤ መንገዱ ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እድገት ካለው ፋይዳ አንጻር አንድ ሊሉ ይገባል። ግንባታው ከተጀመረ በርካታ አመታትን ያስቆጠረው የሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ፤ ግንባታው በአራት ምእራፍ ተከፍሎ በመካሄድ ላይ ያለ ሲሆን፤ ባለፉት በርካታ አመታት ከአራቱ ምእራፎች አንዱ የሆነው ከሞጆ መቂ  ድረስ ያለው የመንገድ ግንባታ ብቻ ከ80 ከመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን፤ የተቀሩት የግንባታ ምእራፎች ግን በተለያዩ ችግሮች የተነሳ እስከአሁን ድረስ ግንባታቸው መድረስ ከምገባው የግንባታ ደረጃ ላይ መድረስ አልቻሉም።   የመንገድ ግንባታው ከአራት የተለያዩ ባንኮች በተገኘ የገንዘብ ወደ 13 ቢሊዮን ብር ብድር እና ድጋፍ የሚሰራ ሲሆን፤ የመንገዱ ግንባታ በዚህ መልኩ መጓተቱ፤ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ካለው አሉታዊ ፋይዳ አንጻር፤ የሁለቱ ክልል መንግስታት ከፌዴራል መንግስት ጋር በመቀናጄት፤ የፍጥነት መንገድ ግንባታው ያጋጠመውን የወሰን አከላለል እና መሰል ችግሮች በመፍታት፤ የሁለቱን ክልሎች ህዝቦች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ስራ ልሰሩ ይገባል።   በተለይ የሲዳማ ክልል መንግስት፤ በክልሉ ካሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለአለም ገበያ የሚቀርቡትን የተለያዩ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርቶችን በከፍተኛ ፍጥነት ለገበያ ለማድረስ ይቻል ዘንድ የዚህ መንገድ መጠናቀቅ ካለው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንጻር፤ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው። ከዚህም በተጨማሪ ከአዲስ አበባ ወደ ሐዋሳ ያለው

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የእንሰሳት ህክምና ሆስፒታልና ማስተማሪያ ህንፃን አስመረቀ

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ማእከል በዚህ መልኩ መገንባቱ፤ በተለይ ለዳቶ ኦዳሄ፣ ጫፌ እና ለሐዋሳ ሀይቅ ዙሪያ የከብት አርብዎች ትልቅ የምስራች ይሆናል።  

Tigrayan Lives Matter more in Ethiopia, one last time

By Samuel Gabisso For many people of Sidama nation, the conflict in Tigray was first felt when their sons serving in the Ethiopian National Defense Force (ENDF) were sent down to Hawassa in body-bags or lost contact with them forever, after the TPLF treasonously massacred its own federal army protecting the border with Eritrea. Since then, the conflict has been mostly hidden as the ENDF quickly defeated the junta and brought them to justice one-by-one. But recently, outside media reports online seem to have provided alternative stories, mostly defending TPLF’s narratives, that should make Sidama and other Ethiopians wonder; where was all this international media the last 29 years?  When we read some of the Western media reports, we can assume that thousands of slain peaceful protestors in Sidama, Oromia, Amhara etc murdered by TPLF the last many years must be rolling over their graves. Whether it is the Looqqe massacre in Sidama or the many others slaughters by TPLF, peacef

በአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ላይ የተደቀነው የፊደል ቀረፃ ችግር

  ዓለም አቀፉ የባህል ተቋም ዩኔስኮ እ.ኤ.አ. በ1999 ባደረገው ጉባዔ፣ የባህልና ቋንቋ ብዝኃነትን ለማሳደግ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ቀን በየዓመቱ የካቲት 14 (ፌብሯሪ 21) ቀን እንዲከበር በወሰነው መሠረት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ እያከበረች የምትገኘው ኢትዮጵያ ለ11ኛ ጊዜ የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰመራ ከተማ ‹‹የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ለትምህርትና ማኅበራዊ ተግባቦት መጠቀምን በማረጋገጥ ልሳነ ብዝኃነትን ማበረታታት!›› በሚል መሪ አክብራለች፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ፣ ቋንቋዎችና  ባህሎች አካዴሚ የሥነ ልሳን ተመራማሪ ተሾመ የኋላሸት (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ትምህርት የሚሰጥባቸው በርካታ ቋንቋዎች ይገኛሉ፡፡ አንዳንዶች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል በአፍ መፍቻ ቋንቋ የሚሰጣቸው ትምህርት የሚያበቃ ሲሆን፣ ሌሎች ደግሞ እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ ብቻ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ይማራሉ፡፡ በአፍ መፍቻ ቋንቋ መሰጠቱ ጠቀሜታው ከፍ ያለ፣ ተማሪዎችም መሠረታዊ ዕውቀት እንዲኖራቸውና የተሻለ ግንዛቤ እንዲይዙ ያግዛል፡፡ በኢትዮጵያ የአፍ መፍቻ ቋንቋ የመማር ማስተማር ሒደት ሲታይ የፊደል ቀረፃ ላይ ችግሮች እንዳሉ የሚናገሩት ተሾመ (ዶ/ር)፣ በተወላጅ ‹‹ፊደል ይቀረፅ›› ሲባል በሙያው ብቁ ባልሆኑ ሰዎች ጭምር እየተቀረፀ በመሆኑ ትልቅ ፈተና መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ትልቁ ችግር ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር ያለመማር ብቻ ሳይሆን፣ የፊደል ቀረፃ በማን ይደረጋል? ምን ያህል ሰዎች ተሳትፈውበታል እንዲሁም ሒደቱ ኅብረተሰቡ ተወያይቶበትና አምኖበት አለመሆኑ ነው፡፡ ይህም በትምህርቱ ላይ ችግር ሊፈጥር ይችላል፡፡ የሥነ ልሳን ምሁሩ ተሾመ (ዶ/ር) ለሪፖርተር እን

አርሶ አደሩን ከመሬት ተጠቃሚ ለማድረግ የሕግና የአተገባበር ችግሮች እንዲፈቱ ምክረ ሐሳብ ቀረበ

  የመሬት ፖሊሲው ለአርሶ አደሩ በመሬቱ የመጠቀም መብት ቢሰጠውም፣ በሕጉም ሆነ በአተገባበሩ ላይ ችግሮች በመኖራቸው አርሶ አደሩ ከመሬቱ የሚገባውን ጥቅም ማግኘት እንዳልቻለ፣ በኦሮሚያ ክልል የተጠና አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ ችግሮቹን ቀረፎ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ የሚቻሉባቸው ምክረ ሐሳቦችም ቀርበዋል፡፡ በመሬት አስተዳደር ላይ የሚስተዋሉ የሕግ፣ የተቋምና የአሠራር ክፍተቶችን ለመሙላት፣ የመፍትሔና የውሳኔ ሐሳብ ማመንጨት ላይ የሚሠራው ላንድ ፎር ላይፍ፣ በኦሮሚያ ክልል መሬት  ላይ የተመሠረተ ኢንቨስትመንት ባሉ ዕድሎች፣ ክፍተቶችና ተግዳሮቶች ዙሪያ ለውይይት መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሑፍ ዓርብ የካቲት 19 ቀን 2013 ዓ.ም. አቅርቦ ነበር፡፡ ጥናቱን ያቀረቡት ጥላሁን ግርማ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የመሬት ጉዳይ በፌዴራል ደረጃ ያልተማከለ ሆኖ ለክልሎች ቢሰምጥም፣ ክልሎች የመሬትን ውሳኔ ጉዳይ ለወረዳ ወይም ለዞን ባለመስጠታቸውና በማዕከል በመያዛቸው በትንሽ መሬት ላይ የሚያርሰው አርሶ አደር ከዕለት ጉርሱ የዘለለ ተጠቃሚ እንዳይሆን አንድ ምክንያት ሆኗል፡፡ አርሶ አደሩ መሬቱን የመጠቀም መብት አለው ብሎ በሕግ ቢቀመጥም፣ ለራሱ ለዕለት ጉርሱ ካልሆነ ከሌሎች ጋር ተቀናጅቶ፣ በራሱ ተነጋግሮና ተደራድሮ ግብርናውንም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ሊያሳድግ ቢፈልግ ሊያሠራ የሚችል መንገድ የለም ብለዋል፡፡ በዳሰሳ ጥናቱ ያሉ ሕጎችና ፖሊሲዎች እንዲሁም ሰነዶች የተዳሰሱ ሲሆን፣ በክልሉ በርካታ ኢንቨስትመንት ያለባቸው አዳማ፣ ቦራ፣ ሎሜ፣ ምሥራቅ ሸዋ፣ ሱሉልታና ፊንፊኔ ዙሪያ ያሉ ወረዳዎች ታይተዋል፡፡ በጥናቱ መሠረት፣ መሬት ላይ የተመሠረተ ኢንቨስትመንት ላይ ያሉት ሕጎች እ.ኤ.አ. በ2005 በአገር ደረጃ ከወጣው የመሬት አስተዳደር ሕግ ጋር ተያይዘው በ2007 ኦሮሚያን ጨ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውኃ ሀብት የግጭት መነሻ መሆኑ እስካልቀረ ድረስ ጥቅም ላይ ሳይውል መፍሰስ የለበትም አሉ

ኢትዮጵያ   ባለችበት   ቀጣና   ውስጥ   ውኃ   የጭቅጭቅ   መነሻ   መሆኑ   አይቀሬ   እንደሆነና   ይህንን   ማስቀረት   እስካልተቻለ   ድረስ   ኢትዮጵያ   ሀብቷን   ጥቅም   ላይ   ሳታውል   ማፍሰስ   እንደማይገባት   ጠቅላይ   ሚኒስትር   ዓብይ   አህመድ  (ዶ/ር)  አሳሰቡ።   ጠቅላይ   ሚኒስትር   ዓብይ   አህመድ  (ዶ/ር)  ሰሞኑን   ከካቢኔ   አባሎቻቸው   ጋር   ባደረጉት   የሥራ   አፈጻጸም   ግምገማ   ላይ   በሰጡት   አስተያየት  ‹‹ ውኃ   በዚህ   በእኛ   ቀጣና   ውስጥ   የጭቅጭቅ፣   የዲፕሎማሲ፣   የግጭትና   የውጊያ   መነሻ   ማዕከል   መሆኑ   አይቀርም ፡፡  ነዳጅን   መተካቱ   አይቀርም ››  የሚል   አስተያየት   ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ   ያሏት   የውኃ   ሀብቶች   በሙሉ   ወደ   ሌላ   አገር   የሚፈሱ   እንጂ   ከሌላ   አገር   ወደ   ኢትዮጵያ   የሚፈስ   አንድም   የውኃ   ሀብት   እንደሌለ የገለጹት   ጠቅላይ   ሚኒስትሩ    የኢትዮጵያን   የተፈጥሮ   የውኃ   ሀብት   በመጠቀም   ረገድ   በመንግሥት   በኩል   ያለው   ዕይታ   የተሟላ   እንዳልሆነ   ገልጸዋል። የኢትዮጵያ   የውኃ   ሀብት   ወደ   ኬንያ፣   ሶማሊያና   ሱዳን   እንደሚፈስ   ለዓብነት   ያነሱት   ጠቅላይ   ሚኒስትሩ   ኢትዮጵያ   ግን   ከአንድም   አገር   ውኃ   የምትቀበል   እንዳልሆነች   ተናግረዋል። ‹‹ ኢትዮጵያ   ከአንድም   አገር   ውኃ   አትቀበልም   ግን   ሰጪ   ናት ፡፡  ይህንን   የምትሰጠውን   ውኃ   ቢያንስ   ተጠቅማበት   የምትሰጥ   አገር   መሆን   አለባት   እንጂ   ዝም   ብሎ   በተፈጥሮ   በተቀደደለት   ቦይ   የሚፈስ   ከሆነ  

ፖለቲካ እና ኩሽ ኩሸቲክ

  ክፍል ፪ የኩሽ ነገድ በመፅሀፍ ቅዱስ እሳቤ በመፅሀፍ ቅዱስ ያለውን የኩሽ አገባብ በርካታ ስራዎች ሲመረምሩት ቆይተዋል። በሀገራችን እንኳ ሩቅ ሳንሄድ ኪዳነወልድ ክፍሌን (1948) እና ተክለፃዲቅ መኩሪያን መጥቀስ ይቻላል። የኤፍሬም ይስሐቅ (1980)  ኩሽ፣ ጁዳይዝም እና ስሌቨሪ  ‘ኩሽ፣ ይሁዲነት እና ባርነት’ የሚለው መጣጥፍ የኩሽን አገባብ በስፋት በመፅሀፍ ቅዱስና በድኅረ-መፅሀፍ ቅዱስ የአይሁድ እምነት ስራዎች ውስጥ የሚመረምር ነው። ኩሽ (እና ከዚህ ስር የወጡ ቃላት) በተለያዩ ቋንቋዎች ባሉት መፅሀፍ ቅዱስ ተመሳሳይ አይደለም። በአንድ ቋንቋ በተለያየ ወቅት በሚገኙ መፅሀፍ ቅዱስ ቅጂዎች ውስጥ እራሱ ልዩነት አለ። በእብራይስጥ ኩሽ የሚለውን በሶስተኛው መቶ ቅጋአ (ቅድመ ጋራ አቆጣጠር) ወደግሪክ የተተረጎመው ብሉይ ኪዳንና ሌሎች የእብራይስጥ ፅሁፎች ላይ በወጥነት ኢትዮጵያ በማለት ቀርቧል። እንደዚሁም፣ ቨልጌት የሚባለው የአራተኛው ክፍለዘመን የላቲን መፅሀፍ ቅዱስ ትርጉምም ኢትዮጵያ በሚል ያቀርበዋል። በእንግሊዝኛው ኪንግ ጀምስ ቅጂ ኢትዮጵያ የሚለውን ከኩሽ ከሚለው ጋር እናገኛለን። ለምሳሌ፣ የካም ልጆችን ሲዘረዝር (ዘፍ 10፡6, 1መዋ 1፡8፣ 1መዋ 1፡9፣ 1መዋ  1፡ 10) ኩሽ ሲል፣ በሌሎች በርካታ ቦታዎች ደግሞ ኢትዮጵያ ይላል። በአማርኛው መፅሀፍ ቅዱስ ያለው ሁኔታም እንደዚሁ ነው። ለምሳሌ፣ በ1962 በወጣው መፅሀፍ ቅዱስ ላይ ኩሽ (ዘፍጥረት 10:6፣ 7 እና 8)፣ ኢትዮጵያ (ዘፍ 2፡13፣ 2መሳ 19፡9፣ አስ 1፡1፣ አስ 8፡9፣ ወዘተ)፣ እንዲሁም ኵሲ (2ሳሙ 18:21፣ 2ሳሙ 18:22፣ 2ሳሙ 18:23፣ 2ሳሙ 18:31፣2ሳሙ 18:32፣ ኢር 36፡14፣ ሶፎ 1፡1) እና ኩዝ (መዝ 7፡መግቢያ [7፡1]) እናገኛለን። ከእብራይስጡ ለመስማማት በእን