Skip to main content

Posts

Showing posts from December, 2020

በሲዳማ ክልል በ1.7 ቢሊዮን ብር የግል ኢንዱስትሪ ፓርክና የዘይት ፋብሪካ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ

  የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አሥረኛ ክልል በሆነው የሲዳማ ክልል በቀን 300 ቶን የምግብ ዘይትና ሌሎች ተዛማጅ ግብዓቶችን ማምረት የሚችል ፋብሪካ ለመገንባት፣ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልሉ ባለሥልጣናት በተገኙበት እሑድ ታኅሳስ 18 ቀን 2013 ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡ ‹‹አማ የኢንዱስትሪ ፓርክ›› የሚል ስያሜ ያለው የኢንድስትሪ ፓርኩ በአቶ አንድነት ጌታቸውና ቤተሰቦቻቸው የተቋቋመ ሲሆን፣ ድርጅቱ ከ2005 ዓ.ም. ጀምሮ በሐዋሳ በ3,500 ካሬ ሜትር ላይ የወረቀትና የወረቀት ማሸጊያ ሲያመርት መቆየቱን፣ በተጨማሪም የምግብ ዘይት ከውጭ አገር አስመጥቶ በማከፋፈል ሥራም  እንደሚታወቅ ተገልጿል፡፡ አማ የሚያስገነባው የኢንዱስትሪ ፓርክ በ100,000 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ሲሆን፣ በውስጡም 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ የሚደረግባቸው ሰባት ፕሮጀክቶችን እንደሚያቅፍ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡ እነዚህም የምግብ ዘይት፣ የፕላስቲክ፣ የካርቶን፣ የሳሙና፣ የጆንያ፣ የቆርቆሮና ሚስማር፣ እንዲሁም የቡና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ናቸው፡፡ በመጀመርያ የሚተከለው የዘይት ፋብሪካው ሲሆን፣ በመጀመርያው ዓመት 100 ቶን ዘይት በቀን እንዲያመርት ታቅዷል፡

Adama CITY 0-0 Sidama Buna Full Highlights l Betking Ethiopian Premier L...

Ethiopia: Hawassa St. Gabriel Annual Celebration | በኮሮና ስጋት ውስጥ የተከበረው የ...

🛑⚽️ሀዋሳ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና ሀይላት እና ጎሎች || Hawassa ketema vs Ethiopia buna Hig...

ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ስፖርት ክለብ ላይ የተጫዋች ተገቢነት ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑ ሲገለፅ ከ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምላሽ እስኪያገኝ ውጤቱ እንደማይፀድቅ ይፋ ሆኗል

ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ስፖርት ክለብ ላይ የተጫዋች ተገቢነት ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑ ሲገለፅ ከ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምላሽ እስኪያገኝ ውጤቱ እንደማይፀድቅ ይፋ ሆኗል ። በሶስተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ (BetKing) ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከ ሀዲያ ሆሳዕና ባደረጉት ጨዋታ የሲዳማ ቡና የዉጪ ዜግነት ያላቸዉ ተጫዋቾች እንዳይሰለፉ ብታገዱም በሀዲያ ሆሳዕና በኩል አምስት ያህል የዉጪ ዜግነት ያላቸዉን በማሰለፍ ጨዋታዉን ማሸነፋቸዉ ይታወሳል፤ በዝህም ምክንያት በማግስቱ ክስ የመሰረተዉ ሲዳማ ቡና ዉሳኔዉን ፌድረሽኑ እስከምታወቅ ጨዋታዉ ዉድቅ እንደምደረግ ዉሳኔ ተላልፏል። በቀጣይ የሚተላለፈዉ ዉሳኔም የሚጠበቅ ይሆናል። በዝሁ ጨዋታ የሲደማ ቡናዉን አጥቂ ይገዙ ቦጋለ ላይ የሀዲያ ሆሳዕናዉ ግብ ጠባቂ በሰራዉ ጥፋት ምክንያት የአራት ጨዋታ ቅጣት ተላልፎበታል። ዉሳኔዉ የሚጸድቅ ከሆነ ሲዳማ ቡና ሶስት ነጥብ እና ሶስት ጎል የሚያገኝ ይሆናል። #ሲዳማ_ቡና_እግርኳስ_ክለብ

Sidamu the 1.7 billion oils of government has been oiled by Fabric Lossar

Hawasi government chairman Qchumira umiha ikkinoha oil is 1.7 billion faabrika lobbying. Ama Biizinisete gaamo draw zayite huuncinanni faabriik raffle harinsho Federaletenna Qoqqowunniti alite massagano basete leelte safote kincho worate amanyoote harissino. Amanyootu beatalara leellinnohu EFDR Daddalunna Industive Ministe Kala Melaku Alle Beli xawisinontee gede Itphiyu aganu aganu aganunni 48 miliyoone beer zayitete fushshitota kule; kuni faabiriki gobbbbled qarra tyrannica assino. Xa nooti zayitete faabirikka goobbate hasatto xibbunni 12 anga calla wonshitanno yiino. Sidamu Dasti Ledamohu Gobbanket police responded to the headquarters of the government; his investigation has been delayed by the previous engineer and the engineer has been removed from the headquarters of Woshshato. Quchumi Gashshoti Line

በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በላቀ ጥራት በመፈፀም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ገለፁ

በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በላቀ ጥራት በመፈፀም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ገለፁ። የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ፀጋዬ ቱኬ እንዲሁም ሌሎች የክልል እና የከተማ አመራር አካላት በሲዳማ ብሔራዊ ክልል በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ተዟዙረው ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ከቴክኒክና ሞያ እስከ ዶሮ እርባታ የሚወስደውና የግንባታ ስራው የተጠናቀቀው የ2 ኪ.ሜ የአስፓልት መንገድ ተመርቆ ለተጠቃሚዎች ክፍት የተደረገ ሲሆን የታቦር ኢኮ ቱሪዝም የልማት ስራዎችም በጉብኝቱ ተዳሰዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሲዳማ ህዝብ ልዩ ምልክት የሆነው እና የግንባታ ስራው በመፋጠን ላይ የሚገኘው የሻፌታ ታወር ህንፃ ግንባታ የተጎበኘ ሲሆን በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀዌላ ቱላ ክፍለከተማ ከፊንጫዋ-ወዮ እስከ ቱላ ዜሮ አንድ እንዲሁም ከገመጦ ጋሌ ማዞሪያ እስከ ቱሎ ቡሹሎ የሚወስደው የአስፓልት መንገድ ግንባታን በይፋ የማስጀመር ስራም ተከናውኗል። በጉብኝቱ ወቅት ንግግር ያፈረጉት አቶ ደስታ ሌዳሞ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳደር በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በላቀ ጥራት በመፈፀም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል። የሲዳማ ህዝብ የአደረጃጀት እና እራስን በራ

በሲዳማ ክልል የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ተደራሽ ለማድረግ የሚረዳ ፕሮግራም በይፋ ተጀመረ

በሲዳማ ክልል የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋንን ተደራሽ ለማድረግ የሚረዳ አሃዳዊ (ዋን ዋሽ) የተሰኘ የመጠጥ ውሀ ፕሮግራም ዛሬ በይፋ ተጀምሯል፡፡ የፌደራል ውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፀጋዬ ዋጌት በክልሉ ያለውን የውሃ አቅርቦት እና ፍላጎት ለማመጣጠን እና የህዝቡን ፍላጎት ለማርካት ፕሮግራሙ አጋዠ በመሆኑ በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። የፕሮግራሙ መጀመር በክልሉ ያለውን ውስን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ ጠቃሚ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ ውሃ እና መስኖ ቢሮ ኃላፊ አቶ ውብሸት ፀጋዬ ናቸው። በቀጣዮቹ አምስት አመታት በዚህ ፕሮግራም 500 ሺህ የሚሆኑ የክልሉ ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላክቷል። (በድልአብ ለማ)  

Sholino 27u diri babbadooshshu poletika soicho agatenni cingiisshino.

Sholino 27u diri babbadooshshu poletika soicho agatenni cingiisshino. ************** vDaggino soorro sufisate 27 diri giddo babbadooshshunna ruukkadimmate poletika toonkanna keeshshitino massagaano soicho agge mucci yaa hoogguro; soorrote guficho ikkitannota yaadigi ei waro qoqqowo sette massaginonna wodiidi qoqqowo sette diro gashshe sainohu kalaa Abaate Kishohu coyi’ri. Kalaa Abaate kishohu Bakkalcho gaazeexii ;ledo assino hasaawinni; IHADEG yinanni dirijjite kaimankanni sarraaqunni safante sakaalante uwansa xawise;xaano hattenne yannara sholino poletika toonkoonnisari soorrote gashshooti giddono hecheemmo kaddanni noori mucuqqi di yitino yino.  27 dirira babbadamooshshe sabbakkanni keeshshitino albisaancho dirijjite Hiwwohaati, ba’’ansa buuxissinohu gargartote olanto aana shigiggissanno gawajjo iillishshu barraati yinohu kalaa Abaate; xaate higgannokkiwa hadhinoha ikkirono insa giggilinna faalensa harunsitannori qoropho assa hasiissanno yiino. ‘’Ayi lasso shii’rinohu; a

በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሀዋሳ ከተማ ታህሳስ 19 ለሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ልዩ ዝግጀት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ

በአዲሱ ክልል ለሚከበረው በዓል ከተማ አስተዳደሩ ከሀይማኖት ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በቂ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በሀዋሳ ከተማ የደብረ- ምህረት ቅ/ገብርኤል ቤተክርስቲያን አስዳዳሪ መላከ ሰላም አባ ኃ/ጊዮርጊስ ማህፀንተ ከተማዋን ከማጽዳት ጀምሮ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በቂ ዝግጅት መደረጉን የገለፁ ሲሆን ለእምነቱ ተከታዮችና ለሚመጡ እንግዶች ሁሉ የ"እንኳን አደረሳችሁ" መልእክት ሲያስተላልፉ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ልዩ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበትም በማስታወስ ነው፡፡  የሀዋሳ ደብረ ምህረት ቅ/ገብርኤል ገዳም የምግባረ- ሰናይ ክፍልና የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲያቆን ፀጋዬ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው በከተማዋ ከሚከበሩ ትላልቅ ሀይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ በሆነው በዚህ በዓል በመንፈሳዊ፣ በማህበራዊ እና በሌሎች ዘርፎችም በተቋቋመ ኮሚቴ አማካይነት በቤተክርስቲያኗ በቂ ዝግጅት መደረጉን ሲገልጹ የዘንድሮው በዓል በአዲሱ ክልል ለየት ባለ መልኩ እንዲከበር አስተዳደሩም ልዩ ትኩረት የሰጠበት መሆኑን አክለዋል፡፡ የሀዋሳ ከተማ አሰተዳደር የሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ መኩሪያ መኒሳ በበኩላቸው ከተማዋ ፍጽም ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት፣ እንግዶቸን ለመቀበል ከየትኛውም ጊዜ በተለየ መልኩ በቂ ዝግጅት የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡ የሲዳማ ህዝብ "ዳኤቡሹ" ብሎ ለመቀበል የተዘጋጀ መሆኑን የገለጹት አቶ መኩሪያ የበዓሉ ተሳታፊዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ፍ/ቤት፣ አቃቤ ህግና የምርመራ አካላት በዓሉ በሚከበርበት አካባቢ በመገኘት አገልግሎት እንደሚሰጡ ተናግረዋል። ታህሳስ 2013ዓ,ም           ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የሀዌላ ቱላ ክፍለከተማ በዳቶና ጨፌ ቀበሌያት የነዋሪውን የመሰረተልማት ጥያቄ ለመመለስ ለመንገድ ከፈታ የተጀመረው የልየታ ስራ 35 በመቶ መድረሱ ተገለፀ

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከ2012 በጀት ዓመት ወዲህ የነዋሪውን የረዥም ጊዜ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በተገቢው ለመመለስ ተግባራዊ እንቅስቀሴ በማድረግ በአጠረ ግዜ ውስጥ ጀምሮ የማጠናቀቅና የማስመረቅ ስራ በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። አቶ አሰፋ አርፋኔ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ም/ስራ አስኪያጅና የከተማ ፕላን ዘርፍ ኃላፊ በ2008 ዓ.ም የመንገድ ከፈታ ስራ ለማከናወን የኤል.ዲ.ፒ ጥናት ተሰርቶ ወደተግባር ያልተገባባቸውና የነዋሪዎች የረዥም ጊዜ ጥያቄ ሆነው ከቆዩ የከተማዋ አካባቢዎች መካከል በ2013 ዓም በሀዌላ ቱላ ክፍለከተማ በዳቶ እና ጨፌ ቀበሌያት የመንገድ ከፈታ ስራ ለመጀመር የልየታ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።  የልየታ ስራው ከፕላን ውጭ ተገንብተው መንገድና ለአረንጓዴ ልማት የሚተው ስፍራዎች የሚነካቸው ነባርና የግዥ ይዞታዎች ተለይተው ተገቢውን ካሳ እና ምትክ ቦታ በማስተላለፍ ለነዋሪዉ የረዥም ጊዜ የመንገድና የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተጀመረ ስራ መሆኑን አቶ አሰፋ ገልፀዋል። የልየታ ስራዉ ከተጀመረ 8ኛ ቀኑን መያዙን የገለፁት አቶ አሰፋ ስራው በቢሮና በመስክ በሁለት ቡድን እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን ከእቅዱ 35 በመቶ መጠናቀቁን ገልፀዋል። ከተማ አስተዳደሩ የነዋሪውን ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ አሰፋ በ2012 በጀት ዓመት የተሰራውን ተመሳሳይ የመንገድ ከፈታ ስራን ጨምሮ ተመርቀዉ አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶች ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን ገልፀው ነዋሪውም የተጀመሩ ስራዎች በተገቢውና በተፈለገው ፍጥነት እንዲጠናቀቁ ህብረተሰቡ የተለመደ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋ

Ethiopian Premier League NewsAshenafi Bekele bemoans Dawa's suspension

  By Emeka Enyadike 23 December 2020 | 03:31 Hadiya Hossana head coach Ashenafi Bekele believes the suspension of star man Dawa Hotessa will be very crucial ahead of the Sidama Bunna tie on round 3 of the BetKing Ethiopian Premier League. Hossana forward Hotessa is suspended for the Sidama Bunna game following his late dismissal when he played against Bahir Dar Ketema and Bekele believes that "To Lose Dawa will be a predicament" Hotessa broke the Covid 19 protocol as he celebrated his last gasp goal against the Waves of Tana with Hossana fans in Addis Ababa. The League Company suspended him for one game and fined him 77 USD. Head trainer Bekele, who happened to work with the striker in Adam Ketema previously, noted his side will have a problem in the Sidama Bunna game. "Dawa is not only Hadiya Hossana's key player. He is also a star and an important player for Ethiopia. We most definitely will miss in the tie and it will be hard for us not to have him against Sidam

Pay cuts and forced overtime: COVID-19 takes heavy toll on Ethiopia's garment workers

HAWASSA, Ethiopia (Thomson Reuters Foundation) - Even before COVID-19 struck, the women stitching clothes at Ethiopia’s Hawassa industrial park were among the world’s worst-paid garment workers - many making less than $30 per month. Today, pay cuts and forced overtime have become common in short-staffed factories abandoned by hundreds of former employees - some too scared of catching the coronavirus to return, several workers told the Thomson Reuters Foundation. Tigist, a 20-year-old seamstress, said some of her colleagues had not come back to Hawassa after they were furloughed in the early months of the pandemic, as the global garment industry was hammered by cancelled orders. In recent months, bosses eager to recover lost business have been forcing the remaining workers to pick up the slack, Tigist - whose name has been changed to protect her identity - and other workers said. “We had to work (more) to fill in the gap,” Tigist said in the tiny, bare room she rents with another worker

በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የአፍሪካን ኢሜጅ የሰርከስ ክበብ

ቤተሰብ ማሳመን የነበረባቸው የሰርከስ አባላት አንደ ኢትዮጲያ ባሉ ሀገራት አዳጊ ሴቶች ከትምህርት ጎን ለጎን ስፓርታዊና ኪነ ጥበባዊ ተሰጥኦዎቻቸውን ለማውጣት በርካታ ቤተሰባዊና ማህበራዊ ጫናዎች እንደሚያጋጥሟቸው ይታመናል።  በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የአፍሪካን ኢሜጅ የሰርከስ ክበብ ውስጥ በአባልነት እየተሳተፉ የሚገኙ አዳጊ ሴቶችም የዚህ ችግር ሰላባ ከመሆን አልዳኑም። ወጣቶቹ የሰርከስ ስፖርት እንዴት እንደጀመሩና በሂደቱ ስላጋጠሟቸው ተግዳሮቶች በ « ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች» #GirlZOffMute ውይይት ገልፀውልናል።  ውይይቱን የመራችው የ17 ዓመቷ ወጣት ሊሻን ዳኜ ናት። ውይይት: ሊሻን ዳኜ ካሜራ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ #girlzoffmute  Hawassa

በተለያዩ ዲዛይነሮች የተዘጋጁ የሲዳማ ባህላዊ አልባሳት ትዕይንት

የአዳሬ ኪነጥበብ ማህበር በሀዋሳ ከተማ ሲዳማ ባህል አደራሽ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቅርቡ ከአፍኒ ኤቨንትስ ጋር በመተባበር የስነጽሁፍና የባህል ምሽት ማዘጋጀቱ የሚታወስ ነው። በመድረኩም በተለያዩ ዲዛይነሮች የተዘጋጁ የሲዳማ ባህላዊ አልባሳት ትዕይንት በመድረኩ ቀርቦ የተመልካችን ቀልብ የሳብ ሆኗል። በአዲሲቷ ክልል ሲዳማ በመሰል የኪነጥበብና ፋሽን ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ድጋፍ ከተደረገላቸው ከዚህ የላቀ ስራ መስራት እንደሚችሉ አቅም እንዳላቸው አሳይተዋል።  የከተማችንን የኪነ ጥበብ ዘርፍም አንድ እርምጃ ወደፊት ያራመደ የኪነ ጥበብ ስራ እንደሆነ ለመመልከት ችለናል።

በሀዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን ትግበራ ዙሪያ

የሀዋሳ ከተማ ም/ከንቲባ ረዳት ፕ/ር አቶ ፀጋዬ ቱኬ በሀዋሳ ከተማ የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን ትግበራ ዙሪያ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የሀቢታት ፕሮጀክት አመራርና ባለሞያዎች ጋር መከሩ፡፡ በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ መድረክ በያዝነው በጀት ዓመት የዝግጅት ስራው ተጠናቆ በሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት የፀደቀውን የሀዋሳ ከተማን የቀጣይ 10 ዓመት መዋቅራዊ ፕላን ወደ ተግባር ለማስገባት በሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡  በመድረኩ በቀጣይ 10 ዓመታት ሀዋሳ ምን መመስል አለባት የሚለውን ጥያቄ ከወዲሁ በተሟላ ደረጃ መልስ ሰጥቶ መሄድ ያስፈልጋል ያሉት ክቡር ከንቲባው በመዋቅራዊ ፕላን ማዕቀፍ ውስጥ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት በማረጋገጥ ሀዋሳ ለኢትዮጵያ ከተሞች ምሳሌ ሆና እንድትቀጥል በትኩረት ይሰራልም ብለዋል፡፡    በመድረኩ የከተማዋን የቀጣይ 10 ዓመት ዕድገት ታሳቢ ባደረገ መልኩ የቤቶች ልማት፣ የሀይቅ ዳርቻዎችን የማስዋብ፣ የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን እንዲሁም የግብይት ስፍራዎችን በአዲስ መልክ ማደራጀት የሚያስችል በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች የተዘጋጀ ፕሮጀክት ፕላን ቀርቦ ሰፊ ውይይትም ተደርጎበታል፡፡  ይህም በመዋቅራዊ ፕላኑ ከተካተቱ ከ8 በላይ የልማት ዕቅዶች ውስጥ ወሳኝ የሆኑ አራቱን ወደ ፕሮጀክት ፕላን በመቀየር ወደ ተግባር ለማስገባት የሚያስችል አቅም የሚፈጥር መሆኑን በመድረኩ የተሳተፉ ባለሞያዎችና አመራር አካላት ገልፀዋል፡፡ አጠቃላይ የመዋቅራዊ ፕላኑ እና የእነዚህ ፕሮጀክቶች ራዕይ በ2030 ሀዋሳ ከተማን "ለኑሮ ምቹ፣ ዘላቂ ልማት የሚካሄድባት፣ የብልፅግና እደዲሁም በኢትዮጵያ እንግዳ ተቀባይ የቱሪስት መዳረሻ" ለማድረግ ያለመ እና የሚያስችል መ

Qoqqowu giddora higge bobbakkanno dureeyye hasattonna kiiro lexxitanni dagganno gede Sidaamu dagoomu qoqqowi investimentete komishine injoo kalaqqanni noota egensiissu.

Qoqqowu giddora higge bobbakkanno dureeyye hasattonna kiiro lexxitanni dagganno gede Sidaamu dagoomu qoqqowi investimentete komishine injoo kalaqqanni noota egensiissu.  ******************************************** Addi addi investimentete latishshuwa loossanni qoqqowoho baadiyyetenna quchummate e’e loosi’rate hasidhanno dureeyye hasattonna kiironsa lexxitanni dagginota Sidaamu dagoomu qoqqowi mootimma investimentete komishine egensiissu.  Sidaamu dagoomu qoqqowi mootimma investimentete komishine; komishinerichi Kalaa Dessaalenyi Meessahu Itophiyu pireesete uurrinshara baxxinohunni Bakkalcho gaazeexira uyino xawishshinni; handaaru loossanni qoqqowu deerrinni investimentete baatto qixxeessine hasiissannota safote latishshuwa injeessine dureeyye rahotenni koyinse loosu giddora eessate ragaanni komishinete biiro umose tantanatenni mittu, ontunna tonnu diri mixo qixxeessi’ne loosu giddora e’noonnita kulino.  Sidaamu giddo baattote gashshooti wodho sa’u yannanni roore woyyeessat

የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሐረሪ እና በሲዳማ ክልሎች ተጀመረ

የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሐረሪ እና በሲዳማ ክልሎች ተጀመረ ******************************  የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሐረሪ እና በሲዳማ ክልሎች ዛሬ ታኅሣሥ 7ቀን 2013 ዓ.ም መሰጠት ተጀምሯል።  ፈተናው በሁለቱም ክልሎች ከታኅሣሥ 7 እስከ 9 እንደሚሰጥ ተገልጿል።  በሐረሪ ክልል 4 ሺህ 213 ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ መቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገልጸዋል።  በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀመጠው ደንብ እና መመሪያ መሠረት የ8ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ኃላፊው ተናግረዋል።  በሲዳማ ክልል 81 ሺህ 277 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተዘጋጁ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።  ፈተናው በደቡብ ክልልም የተጀመረ ሲሆን፣ የፈተና ጊዜው ከዛሬ ታኅሣሥ 7 እስከ 9/2013 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።  በክልሉ 292 ሺህ 769 ተማሪዎች በ3 ሺህ 782 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።  በክልሎቹ የተሰጡት ፈተናዎች ኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ አስፈላጊው ጥንቃቄ ታክሎበት እንሆነ ነው የተገለጸው።  ebc

ሀዋሳ ከተማን የማልማት ፕሮጀክት ይፋ ሊደረግ ነው

"ከተማችንን በጋራ እናልማ" ም/ከንቲባ ረ/ፕ ፀጋዬ ቱኬ   ሀዋሳ ከተማን የማልማት ፕሮጀክት ይፋ ሊደረግ ነው።  ለአንድ ሀገር ልማት መንግስትና ህዝብ በጋራ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ እንጂ መንግስት በሚሰራው ስራ ብቻ ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል እሙን ነው። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ረ/ፕ ፀጋዬ ቱኬ ሀዋሳ ለነዋሪዎቿ ብቻ ሳይሆን ከተማዋን አልፈው ለሚጓዙ ህዝቦችም አሁን ካለችበት በተሻለ ውብና ማራኪ፣ምርጥ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ከጥቁር ውሀ እስከ ሞኖፖል ድረስ 7.5ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን የተለያዪ መዝናኛዎችን ለመስራት መታቀዱን እና እነዚህም አራት ኮሪደሮችን ታሳቢ ያደረጉ ናቸው ብለዋል።  ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋና ጊቢ አከባቢ፣አስተዳደራዊ አከባቢዎች፣የልጆች መጫወቻና መዋያ ቦታዎች እንዲሁም ሁለገብ እንቅስቃሴ ሚደረግባቸው ስፍራዎች የፕሮጀክቱ ዋና ዋና አካሎች ናቸው። ፕሮጀክቱን በዋናነት የከተማ አስተዳደሩ እየመራውና እያማከረ በተጠቀሰው መንገድ ላይ የሚገኙ ተቋማትም አከባቢውን የሚያለሙ መሆኑ ታውቋል። የዚህ ፕሮጀክት ሀሳብ መነሻ ያደረገው ያደጉ ሀገራት ተሞክሮ ሲሆን በውይይቱ ላይ የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት አጠቃላይ ንድፈ ሀሳቡን ተንቀሳቃሽ ምስልን አክሎ በማቅረብ ገንቢ አስተያየቶች ተሰጥቶበታል። በዉይይቱ ላይ የሀዋሳ ዪኒቨርሲቲ፣የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ባለሀብቶች፣የመንግስት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ፕሮጀክቱ ለህዝብ በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ ይሆናል ተብሏል። ሀዋሳ ከ/አ/መ/ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ታህሳስ 7/2013ዓ.       ሀዋሳ

በሲዳማ እየተስፋፋ ያለውን በረሃማነትን ለመከላከል በተፈጥሮ እና በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የተጎዱትን መሬቶች መልሶ የማልማት ስራ ትኩረት ልሰጠው ይገባል

  በሲዳማ ውስጥ በለምለምነታቸው የሚታወቁ አከባቢዎች እንዳሉ ሁሉ፤ በደረቃማነታቸው ሁሌም እንደምሳሌ የምጠቀሱ አከባቢዎችም ሞልተዋል። ከእነዚህ መካከል በተለይ ቦርቻ፣ ቢላቴ ዙሪያ እና አባያ ሎካ ወረዳዎች አንዳንድ ቀበሌያት በደረቅ አከባቢነታቸው እና በጎርፍና በንፋስ ተሽርሽሮ የተጎዱ፣ ቦራቦራማ የመሬት መልካምድር የያዙ አከባቢዎች ናቸው። ለአብነት ያህል በሞሮቾ ታጥፎ በሚገባው እና ወደ ወላይታ ሶዶ በሚውስደው አዲስ መንገድ ዳር እና ዳር በተለይ ወደ ሲዳማ፣ ወላይታ ድንበር ከመድረሱ በፊት ያለው ሰፊ የተንጣለለ ነገር ግን በጣም የተጎዳ መሬት ይታያል። ከዚህ አከባቢ ስደርሱ በተለይ ከምስራቃዊው ሲዳማ አከባቢዎች ወደ አከባቢው የመጣችሁ ከሆነ፤ ሲዳማ ውስጥ ሰለመሆናችሁ ሁሉ ሳትጠራጠሩ አትቀሩም። ይህ መሬት ለዘመናት ከሚመለከተው አካል ትኩረት ስለተነፈገው፤ ይመስለኛል በከፍተኛ ደረጃ የተጎዳ ነው። መሬቱን መሃል ለመሃል አቋርጠው በሚፈሱ የደራሽ ጊዜ ጎርፍ ተሽርሽረው እና ተቆራርጠው በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። በባለፉት አመታት የነበረው መሰል መሬቶችን መልሶ የማልማት ተግባራት፤ በርግጥ በዚህ አከባቢዎች መከናወኑን ባላውቅም፣ መሬቱ እና አከባቢው አሁን ካለው መልክ አንጻር ብዙም መልሶ የማልማት ስራዎች አለመከናወናቸውን በራሱ የሚናገር ይመስለኛል። ይህ ምድር በተለይ በቆሎ ምርት የታወቀ የሲዳማ አከባቢ የነበረ ሲሆን፤ አሁን ግን በርሃማነቱ እየባሰበት በመሄድ ላይ በመሆኑ እና በጎርፍና በንፋስ ተሽርሽሮ የተጎዳውን መሬት መልሶ ለማልማት የሚደረጉ ጥረቶች ባለመኖራቸው፤ ለበቆሎ ምርት ውሎ ሺዎችን መመገብ የሚያስችል መሬት በቆዳ ስፋቱ እያጠረ ይገኛል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው የየወረዳዎቹ አካላት፤ ብሎም የክልሉ መንግስት በሲዳማ በከፍተኛ መልኩ እየተስ

ሲዳማን ሞዴል የማድረጉ ጉዳይ ከምን ደረሰ?

  እንግዲህ የሚያጠግብ እንጀራ ከምጣድ ላይ ያስታውቃል እንደምባለው ሁሉ፣ ምንም እንኳን እንደ ሲዳማ ለክልልነት ድምጻችንን ከሰጠን እንድ   አመት ብቻ ቢሆነውም፤ ብሎም ክልል ከመሰረትን ገና ወራቶችን ብቻ ያስቆጠርን ብሆንም፤ አሁኑ በክልሉ ያሉ ተጨባጭ   እውነታዎች ወዴት እያመራን እንደሆነ የሚጠቁሙ ናቸው የሚል እምነት አለኝ። ነገሩ ከወዲህ ነው። የዛሬ አንድ አመት በህዳር ወር ከወሩ በአስረኛው ቀን፤ ለምእተ ዘመናት እንደህዝብ የታገልንበት ራስን በራስ ማስተዳደሩ ብቻ ሳይሆን፤ የራሳችንን መንግስት ለመመስረት የሚያስችለንን ድምጽ የሰጠንበት እለት ነው። እለቱ በአለም የሚዲያ አውታሮች እንደተዘገበው እና እኛም እንዳየነው፤ ሲዳማውያን እልቅፋቸውን ሳይተኙ አድረው፤ ጠዋት ጸሃይ ጨለማውን እንኳን ሳትገፈው ሰልፍ በመያዝ፣ ህልማቸውን እና የዘመናት ትግላቸውን በድምጻቸው ያረጋገጡበት ቀን ሆኗ አልፋለች። ይች ቀን በሲዳማ ክልል በዚህ አመት እንዴት እንደ የክልሉ የነጻነት ቀን እንዳልተከበረች ባይገባኝም። ቀኗ ግን በሲዳማ ታርክ ውስጥ ካላት ቦታ አንጻር፣ እንደግንቦት 20 በየአመቱ መከበር አለባት ባይ ነኝ። ነገሩ ከወዲህ ነው። የዛሬ አንድ አመት በህዳር ወር ከወሩ በአስረኛው ቀን፤ ለምእተ ዘመናት እንደህዝብ የታገልንበት ራስን በራስ ማስተዳደር ብቻ ሳይሆን፤ የራሳችንን መንግስት ለመመስረት የሚያስችለንን ድምጽ የሰጠንበት እለት ነው። እለቱ በአለም የሚዲያ አውታሮች እንደተዘገበው እና እኛም እንዳየነው፤ ሲዳማውያን እልቅፋቸውን ሳይተኙ አድረው፤ ጠዋት ጸሃይ ጨለማውን እንኳን ሳትገፈው ሰልፍ በመያዝ፣ ህልማቸውን እና የዘመናት ትግላቸውን በድምጻቸው ያረጋገጡበት ቀን ሆኗ አልፋለች። ይች ቀን በሲዳማ ክልል በዚህ አመት እንዴት እንደ የክልሉ የነጻነት ቀን እንዳልተከበ