Skip to main content

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቡና ጥራት ቅምሻ ውድድር በኮሮና ምክንያት ተሰርዞ ወደ አሜሪካ ተዛወረ

በአሜሪካው አሊያንስ ፎር ኮፊ ኤክሰለንስ ድርጅት አዘጋጅነት ለመጀመርያ ጊዜ በኢትዮጵያ እንዲካሄድ ተወስኖ ዝግጅት ሲደረግበት የከረመው የቡና ጥራት ውድድር ወይም ‹‹ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ›› ውድድር በኮሮና ምክንያት በተፈጠረ የበረራ ክልከላና በሎጂስቲክስ ችግሮች ምክንያት ተሰርዞ በአሜሪካ እንዲካሄድ መወሰኑ ታወቀ፡፡
አሊያንስ ፎር ኮፊ ኤክሰለንስ እንዳስታወቀው ከሆነ፣ በኢትዮጵያ ሊካሄድ የታቀደው የቡና ጥራት ቅምሻ ውድድር በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ዳኞች አወዳዳሪነት እንዲካሄድ ሰፊ ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በውድድሩ ታሪክ ከፍተኛ የቡና ናሙና በማቅረብ የኢትዮጵያ ቡና አምራቾች ሪከርድ የሰበሩበትን ተሳትፎም አስተናግዶ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተጎጂዎችን ያጠቃውና ከ60 ሺሕ በላይ ለሞት የዳረገው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የዓለም ኢኮኖሚ በማሽመድመድ ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ ዝግጅት ሲደረግበት የሰነበተውና ዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጠው የቡና ጥራት ውድድርም የኮሮና ሰለባ ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣንና በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (ዩኤስኤአይዲ) ሥር ፊድ ዘ ፊውቸር የተሰኘው ተቋም ሲያስተባብሩት የቆየው ዝግጅት ወደ አሜሪካ እንዲዘወር መደረጉን አዘጋጁ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በመሆኑም የቡና ጥራት የቅምሻ ውድድሩ በፖርትላንድ፣ ኦሪገን እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡
ምንም እንኳ የመጨረሻው የጥራት ውድድር በበረራ ክለከላና በሎጂስቲክስ ችግሮች ምክንያት በኢትዮጵያ ባይካሄድም፣ ለውድድሩ የቀረቡ ናሙናዎች ወደ አሜሪካ ተልከውና በላቦራቶሪ ተፈትሸው አሸናፊዎቹ ናሙናዎች ለባለቡናዎቹ እንዲገለጹ የሚደረግበት ተለዋጭ ዕቅድ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡
ለዚህ ተግባር የሚጠበቁ ዳኞችን በሙሉ ማሳተፍ ባይቻልም፣ የተመረጡና ልምድ ያላቸው የዳኞች ስብስብ ከኢትዮጵያ የተላኩትን የቡና ናሙናዎች እንደሚመዝኑም ተገልጿል፡፡
ከሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፣ በጥራት ቅምሻው ውድድሩ  ላይ  ለመሳተፍ  ከጥር  25  ቀን  እስከ  ጥር  29 ቀን  2012  . በጅማ፣  በሐዋሳ፣  በድሬዳዋና በአዲስ  አበባ ለውድድር  የሚቀርቡ  ቡናዎችን  ለመሰብሰብ  ወደተዘጋጁ  ማዕከላት  1,450 በላይ የቡና ናሙናዎች  ገቢ  ተደርገው ነበር፡፡ 
ኮሮና ቫይረስ ያጠላበት ይህ ውድድር ከፍተኛ የቡና ናሙና ለውድድር የቀረበበትና  ባለፉት  20  ዓመታት  ውስጥ  ለመጀመርያ  ጊዜ  የቀረበ  ከፍተኛው  አኃዝ ቢሆንም፣ በወረርሽኙ ሥጋት ምክንያት በኢትዮጵያ ብቻም ሳይሆን፣ በሌሎች ከአሥር ያላነሱ አገሮች ሊካሄድ የታቀደው የቡና ቅምሻ ውድድር ሊሰረዝ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ የጥራት  ቅምሻ  ውድድሩ  በ11 ቡና  አምራች  አገሮች  ውስጥ  ሲካሄድ  ቆይቷል፡፡ 
የባለልዩ  ጣዕም  ቡናዎች  የጥራት  ውድድር  ላይ  እስካሁን  ከተመዘገበው  ይልቅ  ለመጀመርያ  ጊዜ  የታየና  ከፍተኛ  ቁጥር  ያለው  የቡና  ናሙና  ቀርቧል፡፡
ውድድሩ  .. 1999  በብራዚል  ተጀምሮ፣  በኮሎምቢያ፣  በፔሩ፣  በኤልሳልቫዶር፣  በኮስታሪካ፣  በኒካራጓ፣  በጓትማላ፣  በሆንዱራስ፣  በሜክሲኮ፣  በብሩንዲና  በሩዋንዳ  ሲካሄድ  ቆይቷል፡፡ የኢትዮጵያ  የቡና  ጥራት  በዓለም  አቀፍ  ዳኞችና  በኢትዮጵያውያን  ተሳትፎ  የሚካሄድ  የልዩ  ጣዕም  ቡናዎች  የቅምሻ  ውድድር  ወደ  ኢትዮጵያ  አምጥቶ ነበር፡፡ ተወዳዳሪዎች  በተለይም  ቡና  አምራች  ገበሬዎች  በጥንቃቄ  ጥራት  ያለው  ቡና  እስካቀረቡ  ድረስ  የተሻለ ዋጋ  እንደሚያገኙ  ይጠበቃል፡፡  አቀናባሪዎችና  ሌሎችም  የቡና  ኢንዱስትሪ  ተሳታፊዎች  የተሻለ  ገበያና  ዋጋ  እንደሚያገኙ  ስለሚታመን  በውድድሩ  ተጠቃሚዎች  እንደሚሆኑ  ከሚጠበቁት  መካከል  ናቸው፡፡  ውድድሩ  የዓለም  የቡና  ኢንዱስትሪ  ተዋንያንና  ሚዲያዎችን  ትኩረት  ስለሚስብ  ዕውቅ የኢትዮጵያ ቡናዎች  የበለጠ  ዕውቅና  ማግኘት  የሚችሉበት  አጋጣሚ  ይፈጠራል፡፡ ቡናና  ሻይ  ባለሥልጣን  ከዚህ ቀደም እንዳስታወቀው፣  የውድድሩን  የመጀመርያ  ዙር  የሚያልፉ  ናሙናዎች  ወደ  አዲስ  አበባ  ተልከው  በአገር  ውስጥ  ቀማሾች  የጥራት  ደረጃቸው  ይለካል፡፡  ከእነዚህ  ቡናዎች  ውስጥ  150 አሸናፊዎች  ተመርጠው  በአገር  ውስጥ  ቀማሾች  በድጋሚ  ተቀምሰው፣  40  የላቁ  ቡናዎች  ለመጨረሻ  ዙር  ውድድር  ያልፋሉ፡፡ ውድድሩን  የሚዳኙት ከመላው  ኢትዮጵያ  ተውጣጥተውና  ተገቢውን  ሥልጠና  ወስደው  ብቃታቸው  የተረጋገጠላቸው  ዳኞች  ሲሆኑ፣  ከተለያዩ  አገሮች  የሚሳተፉት  ዳኞችም በሌሎች  አገሮች  የተካሄዱ  ውድድሮች  ላይ  የተሳተፉና  የዳኙ፣  ልምዱና  ዕውቀቱ  ያላቸውን  ቡና  ገዥዎችና  ዳኞችን  ያካተተ  ስብስብ  ስለመሆኑ የባለሥልጣኑ  መረጃ  ይጠቅሳል፡፡
በጥራታቸው  አሸናፊ  የሚሆኑ  ቡናዎች፣  ውድድሩ  በተካሄደ  በስድስት  ሳምንት  ጊዜ  ውስጥ  በካፕ  ኦፍ  ኤክሰለንስ  ድረ ገጽ  አማካይነት  በሚከናወን  ዓለም  አቀፍ  ጨረታ  አማካይነት  ለገዥዎች  እንደሚሸጡ  ይጠበቃል፡፡ ከዚህ  ቀደም  በተደረጉ  ውድድሮች  በጥራት  አሸንፈው  የተሸጡ  ቡናዎች  በተደጋጋሚ የዓለም  የቡና  ዋጋ ሪከርድ  መስበራቸው  ይጠቀሳል፡፡  ከየካቲት  16  ቀን  እስከ  የካቲት  20  ቀን  2012  . ድረስ  ለውድድር  በገቡት  ቡናዎች  ላይ የቅድመ  መረ  ሥራ  እንደሚከናወን፣  ቡናዎችን  ወደ  መጋዘን  የማስገባት  ሥራውም  ከየካቲት  23  ቀን  ጀምሮ እስከ መጋቢት  14  ቀን  2012  .እንደሚከናወን፣  አገር  አቀፍ  ውድድሩም  ከመጋቢት  21  ቀን  እስከ  መጋቢት  25  ቀን  2012  . እንደሚካሄድ  ብሎም  ዓለም  አቀፍ  የውድድር መድረኩ  ከመጋቢት  29  ቀን  እስከ  ሚያዝያ  2  ቀን  2012  ..  እንደሚከናወን  ይጠበቅ ነበር፡፡  ዓለም  አቀፍ  የሽያጭ  ጨረታው  በግንቦት እንደሚካሄድ  ባለሥልጣኑ  ይፋ  ማድረጉን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግን የዚህ ውድድርና የሽያጭ መርሐ ግብር ብቻም ሳይሆን፣ ከአገሪቱ ለውጭ ገበያ የሚቀርበው የቡና ምርትም ከፍተኛ የገበያ ችግር ተጋርጦበታል፡፡ ሥጋታቸውን ከወዲሁ ለሪፖርተር የገለጹ ላኪዎች በበሽታው ወረርሽኝ ሳቢያ በርካታ አገሮች የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ላይ ገደብ እየጣሉና ዕገዳ እያወጡ በመሆናቸው ሳቢያ፣ የዘንድሮው የቡና የወጪ ንግድ ከባድ አጣብቂኝ ውስጥ ሊገባ እንደሚችል ሥጋት አድሮባቸዋል፡፡ በዚህ ዓመት ከ300 ሺሕ ቶን ያላነሰ የቡና ምርት ለውጭ ገበያ ቀርቦ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ሊገኝ መታቀዱ ይታወቃል፡፡ 
በቅርቡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ይፋ ባደረገው መረጃ፣ በስምንት ወራት ውስጥ ለውጭ ከቀረበ ከ167 ሺሕ ቶን በላይ የቡና ወጪ ንግድ ከ465 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ገቢ መገኘቱ ታውቋል፡፡ ከታቀደው የገቢ መጠን ከ100 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ ቅናሽ አስተናግዷል፡፡
ባለሥልጣኑ ለሪፖርተር ልኮ በነበረው መግለጫ መሠረት፣ ለውጭ ገበያ የቀረቡት ቡናን ጨምሮ የሻይና የቅመማ ቅመም ምርቶች ሲሆኑ፣ በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት ውስጥ 176,249.80 ቶን የቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ውጤቶችን በመላክ 577.70 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የዕቅዱን 100 በመቶ ያሳካበትን የ176,360.82 ቶን ምርት አፈጻጸም በማስመዝገብ የምርት አቅርቦቱን ቢያሳካም፣ በገቢ ረገድ ግን የሁሉም ምርቶች ውጤት ከ478 ሚሊዮን ዶላር ወይም የዕቅዱን 81 በመቶ ያህል ገቢ አስገኝቷል፡፡
ከዚህ አፈጻጸም ውስጥ የቡና ድርሻ በምርት ብዛት መጠን 167,132 ቶን ነበር፡፡ ከዕቅድና ከአፈጻጸም አኳያ ሲዘመን፣ ከ2011 .ስምንት ወራት አኳያ፣ በመጠን ረገድ የ37,893.22 ቶን ወይም የ27.37 በመቶ፣ በገቢ በኩልም የ28.2 ሚሊዮን ዶላር ወይም 6.3 በመቶ ጭማሪ ማስመዝገቡ ተጠቅሷል፡፡
በስምንት ወራት ከተላከው የቡና ምርት ውስጥ 138 ቶን ቡና እሴት ተጨምሮበት ለውጭ ገበያ ሲቀርብ፣ ከገቢ አኳያም ከ900 ሺሕ ዶላር ገደማ አስገኝቷል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa