Skip to main content

ከዘጠኙ ክልሎች አራቱ ብቻ ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ዝግጁ መሆናቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ

በኢትዮጵያ በፊትም በአንፃራዊነት የተሻለ የጤና አገልግሎት ደረጃ ያላቸው አራቱ ክልሎች ብቻ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ዝግጁ እንደሆኑ፣ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ ያደረገው ግሞገማ አመለከተ።
የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በተቀመጠው ዓለም አቀፍ መመዘኛ መሥፈርቶች መሠረት ከተመዘኑት ዘጠኙ የክልል መንግሥታት መካከል አራቱ ዝቅተኛውን የዝግጅት ደረጃ እንዳሟሉ፣ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ መገምገሙን ሪፖርተር ያገኘው የሰነድ መረጃ አመልክቷል።
ቢሮው የግምገማውን ውጤት የያዘ ሪፖርት ለባለድርሻ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቋማት፣ በተጠናቀቀው እ.ኤ.አ. ማርች ወር ላይ ማቅረቡን መረጃው ያመለክታል። አገሮች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ የዓለም ጤና ድርጅት ዘጠኝ መሠረታዊ መሥፈርቶችን ያስቀመጠ ሲሆን፣ በእነዚህ መመዘኛ መሥፈርቶች ድምር ውጤት መሠረት ከ80 በመቶ በላይ ያመጡ ዝግጁ ተብለው እንደሚቆጠሩ ከመረጃው ለመረዳት ተችሏል።
በእነዚህ መመዘኛ መሥፈርቶች ተገምግመው ከ80 በመቶ በላይ ያመጡት ክልሎች ኦሮሚያ፣ አማራ፤ ደቡብና የትግራይ ክልሎች መሆናቸውን መረጃው ያመለክታል። በዚህም መሠረት ኦሮሚያ 82.7 በመቶ፣ አማራ 80.9 በመቶ፣ ደቡብ 94.5 በመቶና ትግራይ 85.5 በመቶ በማግኘት ወረርሽኙን ለመከላከል ዝግጁ እንደሆኑ ሪፖርት ማድረጋቸውን መረጃው ያመለክታል።
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ የክልል መንግሥታቱ የሚገኙበትን የዝግጅት ደረጃ የገመገመው የክልሎቹ ተቋማት ለእያንዳንዱ የመመዘኛ መሥፈርቶች የሰጡትን ምላሽ መሠረት በማድረግ እንጂ፣ በራሱ ሄዶ በማጣራት ያደረገው  እንዳልሆነ በሰነዱ ተመልክቷል፡፡
ጥቅም ላይ በዋሉት ዘጠኙ መመዘኛ መሥፈርቶች የቫይረሱ ሥርጭትን መከላከልና መቆጣጠር፣ ቅኝት የማድረግ አቅም (ሰርቪላንስ)፣ ለቫይረሱ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የተቋቋመ ቡድን ማዘጋጀት፣ የቫይረሱ ሥርጭት ሥጋትን የማሳወቅ አቅም፣ የቫይረሱ መግቢያ በሮች ላይ የሚደረግ የጥንቃቄ ዝግጅት፣ የመመርመር አቅም፣ የሎጂስቲክስ ዝግጅትና ኬዝ ማኔጅመንት ወይም ለወረርሽኙ ምላሽ የሚሰጥበት የዝግጅት ደረጃ (ማለትም የሰው ኃይል አቅም፣ የመለያ ማዕከል፣ ሕክምና መስጫ ማዕከል)፣ እንዲሁም ተቀናጅቶ የመሥራት ዝግጅት ናቸው።
በእነዚህ መመዘኛዎች ተገምግመው ከ80 በመቶ በላይ አጠቃላይ ውጤት ካመጡት አራት ክልሎች ውጪ፣ የተቀሩት ክልሎች በተለያዩ የዝግጅት ደረጃዎች ላይ መሆናቸውን መረጃው ያመለክታል። በመመዘኛ መሥፈርቱ የዝግጅት ደረጃ አሰጣጥ መሠረት የአጠቃላይ መሥፈርቶቹ ድምር ውጤት ከዜሮ እስከ 49 በመቶ ከሆነ ዝግጁ እንዳልሆኑ የሚቆጠር ሲሆን፣ ከ50 እስከ 79 በመቶ ያስመዘገቡት ደግሞ ውስን የዝግጅት ደረጃ ያላቸው ተብለው ይመደባሉ።
በዚህ መሠረት፣ አፋር፣ ቤንሻንጉል ጉምዝ፣ ጋምቤላና ሐረሪ (የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጨምሮ) ክልሎች ውስን የዝግጅት ደረጃ የተሰጣቸው ሲሆን፣ ክልሎቹ በተገለጹበት ቅደም ተከተል መሠረት 78.2 በመቶ፣ 59.1 በመቶ፣ 51.8 በመቶና 62.7 በመቶ ደረጃ እንደተሰጣቸው መረጃው ያመለክታል።
ከሁሉም በታች በዝቅተኛ የዝግጅት ደረጃ ላይ የሚገኘው የሶማሌ ክልል ሲሆን፣ አጠቃላይ ውጤቱ 27.3 በመቶ በመሆኑ ዝግጁ ያልሆነ ደረጃ ተሰጥቶታል። የምዘና ሪፖርቱ የሶማሌ ክልልና ሌሎቹ በውስን ዝግጅት ደረጃ ላይ የሚገኙ ክልሎች ፈጣን ምላሽ፣ እንዲሁም ዕገዛ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ያሳስባል።
 ነገር ግን ሁሉም ክልሎች የተለያየ የዝግጅት ደረጃ ላይ ይገኙ እንጂ፣ ሁሉም ክልሎች በተናጥል መሥፈርቶቹ ሲመዘኑ በቂ ዝግጅት ላይ አለመሆናቸውን ሰነዱ ይገልጻል። በተለይም ከዘጠኙ መሥፈርቶች ውስጥ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንደ ዋነኛ መመዘኛ ከሚያገለግሉት መካከል ኬዝ ማኔጅመንት፣ የቫይረሱ ሥርጭትን መከላከልና መቆጣጠር (IPC)፣ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ቡድን ማቋቋምን ከሚመለከቱት መሥፈርቶች አንፃር ሁሉም ክልሎች በዝቅተኛ የዝግጅት ደረጃ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው፣ ፈጣን ማስተካከያ ካልተደረገ አሳሳቢ መሆኑ በሰነዱ ተመልክቷል።
የጤና ሚኒስቴርና የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋራ ሆነው የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት የተመለከተ ግምገማ የተለያዩ የቢሆን መመዘኛዎችን (Scenarios) በመጠቀም፣ ግርድፍ የጉዳት መጠኖችን እንደለዩ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ከእነዚህ ቢሆኖች አንዱ የከፋ ጉዳት ቢሆን (Worst Case Scenario) መመዘኛ ሲሆን፣ ይህም ማለት ምንም ዓይነት የተለየ ዝግጅት ባልተደረገበት፣ በነባሩ የጤና አገልግሎት ዝግጅትና የማኅበረሰብ እንቅስቃሴና የአኗኗር ዘይቤ ሳይቀየር የቫይረሱ ሥርጭት ምን ሊሆን እንደሚችል የተገመገመበት ነው።
በዚህ የሁለቱ ተቋማት ግምገማ መሠረት ለቫይረሱ የመጋለጥ ምጣኔ (ሥርጭት) በገጠርና በከተማ ተለይቶ የተቀመጠ ሲሆን፣ የሁለቱ ድምር በርካታ ሕዝብ ለቫይረሱ ተጋላጭ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል።
ተጋላጭ ማለት የተጠቀሰውን ያህል ሕዝብ በቫይረሱ ያጠቃል ማለት እንዳልሆነ ዳሰሳው ያመለክታል። ሁሉም የመንግሥት አካላት ፈጣንና ጠንካራ የመከላከልና የመቆጣጠር ዝግጅት ካደረገና ማኅበረሰቡም የሥጋት ደረጃውን ተገንዝቦ የጥንቃቄ ዕርምጃዎችን በአግባቡ የሚተገበር ከሆነ፣ የተጋላጭነት መጠኑም ሆነ በቫይረሱ ሊጠቃ የሚችለውን የሰዎች ብዛት መቀነስ እንደሚቻል በመረጃው ተብራርቷል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa