Skip to main content

ፓርላማው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባቀረበለት የምርጫ ውሳኔ ሐሳብ ላይ ለውሳኔ ሊሰበሰብ ነው

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመጪው ነሐሴ ወር ሊካሄድ ታስቦ የነበረውን አጠቃላይ ምርጫ በተመለከተ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ መክሮ ውሳኔ ለማሳለፍ፣ ሐሙስ ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ይሰበሰባል።
ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አንድ የሪፖርተር ምንጭ እንደገለጹት፣ የፓርላማው ስብሰባ የሚያተኩረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮ አጠቃላይ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በመጪው ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ለማካሄድ እንደማይችል በመግለጽ፣ ፓርላማው ውሳኔ እንዲሰጥበት ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተወያይቶ ለመወሰን ነው።
በዚሁ መሠረት ምርጫ ቦርድ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ምርጫውን ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ማካሄድ እንደማይችል ያቀረባቸውን ዝርዝር ምክንያቶች፣ እንዲሁም ቦርዱ ለፓርላማው የመፍትሔ ውሳኔ መነሻ ከሆነ ብሎ ያሰናዳውን በዳሰሳ ጥናት ላይ የተመሠረተ የቢሆን መፍትሔ አማራጭ በምክር ቤቱ በአካል ተገኝቶ እንደሚያቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በሌላ ጊዜ ለማካሄድ በመፍትሔ አማራጭነት የሚያቀርባቸውን ሐሳቦች ምክር ቤቱ ካዳመጣ በኋላ፣ በሕገ መንግሥቱ ዓውድ ውስጥ ተገቢ የሚሆነው ሕጋዊ ውሳኔ ሊወሰን እንደሚችል ይጠበቃል።
 የፓርላማው የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት በመጪው ሐሙስ መደበኛ ስብሰባ እንደሚካሄድ ለሪፖርተር የገለጸ ቢሆንም፣ ውይይት ስለሚደረግበት አጀንዳ ግን መረጃ እንደሌለው አስታውቋል።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው መግለጫ የኮሮና ወረርሽኝ መከሰት በፈጠራቸው ተግዳሮቶች፣ እንዲሁም በዚህ ምክንያት የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ባወጧቸው ክልከላዎች ምክንያት ምርጫውን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ማከናወን እንደማይችል ማስታወቁ ይታወሳል።
በዚህ የተነሳም ለምርጫው የተዘጋጀውን የጊዜ ሰሌዳ በመሰረዝ መከናወን ያለባቸው የምርጫ ዝግጅት ተግባራት ለጊዜው እንዲቆሙ መወሰኑ አይዘነጋም። በማከልም በሕገ መንግሥቱ በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት በሥራ ላይ የሚገኘው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥልጣን ጊዜው ከሚያበቃበት አንድ ወር አስቀድሞ ቦርዱ አጠቃላይ ምርጫውን ማድረግ የማይችል መሆኑን ሕዝብ ተገንዝቦ፣ ውሳኔ እንዲሰጥበት ምክረ ሐሳብ እንዳቀረበም በዚሁ በመግለጫው ማመልከቱ እንዲሁ።
 ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ምክር ቤቱ የሥልጣን ጊዜው ከማብቃቱ በፊት ውሳኔ እንዲሰጥበት የጠየቀው፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 58(2) መሠረት የምክር ቤቱ የሥልጣን ዘመን አምስት ዓመት በመሆኑና በሥራ ላይ ያለው ምክር ቤት የሥልጣን ዘመን በዚሁ ድንጋጌ መሠረት በሰኔ ወር 2012 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ የሚጠናቀቅ በመሆኑ ነው።
የምክር ቤቱ የሥልጣን ዘመን ከማብቃቱ በፊት አጠቃላይ ምርጫ ተካሂዶ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ሥልጣን የሚይዘው አዲስ ምክር ቤት ካልታወቀ፣ በአሁኑ ወቅት ሥልጣን ላይ የሚገኘው ምክር ቤትም ሆነ በእሱ የተመሠረተው መንግሥት በሥልጣን ላይ መቀጠል የማይችሉ በመሆናቸው የሥልጣን ክፍተት እንደሚያጋጥም የሕግ ባለሙያዎች ይገልጻሉ።
የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ደግሞ በየአምስት ዓመቱ አጠቃላይ ምርጫ እንደሚካሄድ ካስቀመጠው ድንጋጌ ውጪ ምርጫ ማከናወን የማይቻልበት ከአቅም በላይ የሆነ እክል ቢያጋጥም ምርጫ ማራዘም ስለሚቻልበት፣ ወይም የሥልጣን ክፍተቱ እንዴት ሊሞላ እንደሚችል የሚያስቀምጠው ድንጋጌ አለመኖሩን ያስረዳሉ።
 በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 60 ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫ ለማካሄድ ሲባል በሥራ ላይ ያለውን ፓርላማ የሥልጣን ዘመን ከማብቃቱ በፊት እንዲበተን የውሳኔ ሐሳብ በማቅረብ፣ በምክር ቤቱ በሚሰጠው ውሳኔ ምክር ቤቱ የሚበተንበት ሥነ ሥርዓት ተደንግጓል።
 በዚህ መንገድ ምክር ቤቱ በተበተነ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ምርጫ እንደሚካሄድና በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥትም ምርጫውን ከማስፈጸምና የዕለት ተዕለት አገር የማስተዳደር ተግባር ውጪ፣ ሕግ ማውጣትም ሆነ መሻር እንደማይችል በዚሁ አንቀጽ ሥር ባሉ ንዑስ አንቀጾች ተደንግጓል።
አንዳንድ የሕግ ባለሙያዎች ይኼንን አንቀጽ በመጠቀም አሁን ያጋጠመውን ሁኔታ ማለፍ እንደሚቻል ቢገልጹም፣ ሌሎች የሕግ ባለሙያዎች በበኩላቸው ይህ አንቀጽ የተቀመጠው በምርጫ የተመሠረተ መንግሥት የሥልጣን ዘመኑ ጅማሮ ወይም መካከል ላይ ቅቡልነቱን ቢያጣ አዲስ ምርጫ (Snap Election) ለማካሄድ እንጂ፣ የምርጫ ጊዜን ለማራዘም እንዳልሆነ ይከራከራሉ። የተለየ ሐሳብ የሚያንፀባርቁ የሕግ ባለሙያዎች በበኩላቸው አሁን በተፈጠረው የቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከመጠናቀቁ አስቀድሞ፣ ለተጨማሪ ስድስት ወራት እንዲራዘም በማድረግ ምርጫው እንዲገፋ ማድረግ እንደሚቻል ይገልጻሉ።
እነዚህ ባለሙያዎች ይህንን አማራጭ የሚያነሱት አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ማድረግ፣ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት (ከአራት አንቀጾች ውጪ) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እስኪያበቃ ድረስ ተፈጻሚነት እንዳይኖረው የሚያደርግ ውጤትን የሚያስከትል በመሆኑ ነው። ነገር ግን ይህ ሐሳብ በሌሎች የሕግ ባለሙያዎች ተቀባይነት የለውም።
ምክንያቱ ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንድ የገጠመን እክል ለማለፍ ጥቅም ላይ የሚውል እንጂ፣ ምርጫን ለማራዘም የሚሠራ አለመሆኑንና ሥልጣንን ያላግባብ እንደ መጠቀም እንደሚቆጠር ይገልጻሉ።
አሁን ከምርጫው ጋር ተያይዞ የገጠመው ችግር የሕገ መንግሥቱ ውስንነት መሆኑን አምኖ መቀበል እንደሚያስፈልግ፣ ምርጫውን ለማራዘም ሌሎች የሕገ መንግሥት ድንጋጌዎችን እንደ አማራጭ መጠቀም ድንጋጌዎቹን ከመሠረታዊ ዓላማቸው ውጪ ሥልጣን ለማራዘም እንዲውሉ ማድረግ መሆኑን፣ ይህንን ማድረግም ‹‹ሥልጣንን ያላግባብ እንደ መገልገል (Abuse of Incumbency) ይቆጠራል›› ይላሉ፡፡
በመፍትሔነት የሚያነሱት ደግሞ የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 58(2) ማሻሻል ነው፡፡ ሚዛን የሚደፋ ከሆነ የተባለውን አንቀጽ ለማሻሻል በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 105(2) መሠረት የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች በጋራ ስብሰባ ማሻሻያውን በሁለት - ሦስተኛ ድምፅ ማፅደቅ፣ እንዲሁም ከዘጠኙ ክልሎች የክልል ምክር ቤቶች ሁለት - ሦስተኛዎቹ ማሻሻያውን በአብላጫ ድምፅ ማፅደቅ ይኖርባቸዋል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa