Skip to main content

Posts

Showing posts from February, 2020
ለደቡብ ክልል አፈ-ጉባዔ ጽ/ቤት ሀዋሳ፤ ጉዳዩ፡- በህገ-መንግስቱ መሠረት የሥልጣን ርክክብ እንዲደረግ ስለማሳሰብ፤ ========= አንደሚታወቀው ሁሉ የሲዳማ ህዝብ ለዚህች አገር ሰላም፣መረጋጋትና አንድነት የራሱን የታሪክ አሻራ ያኖረና በአንፃሩም ደግሞ በየዘመኑ የሚፈራረቁ አምባገነን የኢትየጵያ ገዢዎች የሚያደርሱበትን በደልና አፈና በጽናት ስታገል የቆየ ህዝብ እንደሆነ ታሪካዊ ሀቅ ነው፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የሀገሪቷን ሥልጣን ኮርቻ የሚቆናጠጡ ገዢዎች ሲዳማን ሳይሆን የሲዳማን ሀብት ለመቀራመት ካላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የህዝቡን ቋንቋ፣ታሪክ፣ ባህልና ማኅበራዊ አሻራና ማንነት ለመናድ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡የሀገር ግንባታ ሂደት የማንነት ፈተና በማይሆንበት መልኩ መስራት ይቻላል የሚል ጠንካራ አቋም ማራመድ የጀመሩት የሲዳማ ቀደምት ታጋዮችና ሌሎች የትግል አርበኞች በከፈሉት የህይወት ዋጋ ላለፉት 28 አመታት ስራ ላይ የዋለው ህገ-መንግስታዊ ሥርዓት እውን ሆኗል፡፡ ምንም እንኳን የሲዳማ ህዝብ የጭቁን ብሔሮችን ድምጽ አስተጋብቶና ታግሎ ለ1987 ዓ.ም ህገ-መንግስት ታሪክ የማይረሳ አሻራውን ለማሳረፍ ቢበቃም የሲዳማ ምድር እንጅ የሲዳማ ህዝብን አምርረው በሚጠሉ ገዢ መደቦች በተጠነሰሰ ሴራዎች ህዝባችን የህገ-መንግስቱ ትሩፋት ተቋዳሽ እንዳይሆን በመታገዱ ምክንያት ለቀጣይ ሰላማዊ የትግል ምዕራፍ ለመቀጠል ተገዶአል፡፡ በገዛ ሀገሩ ወደ ዳር የተገፋና በይ ተመልካች ሆኖ ለዘመናት የቆየው ሰፊው የሲዳማ ህዝብ በደሙና ባጥንቱ የተጻፈው ህገ-መንግስት ሊታደገው ባለመቻሉ ለሞት፣ ለስደትና ለእስራት ቢዳረግም ቅሉ ህዝብን ግን ከትግል ወደ ኋላ ሊያስቀረው አልቻለም ፡፡ በመሆኑም ከአባቶች የተወረሰ መብትን የማስከበር የትግል ወኔ ለዚህ ዘመን ትውልድ በመድረሱ አዲሱ ትውልድም የትግል

“ኤጄቶ የለወጥ ሃይል እንጂ አልቃይዳ ወይም አልሸባብ አይደለም”፤ ዛሬ ከእስር የተፈቱ የኤጄቶ መሪዎች

ኤጄቶ የለወጥ ሃይል እንጂ አልቃይዳ ወይም አልሸባብ አይደለም”፤ ዛሬ ከእስር የተፈቱ የኤጄቶ መሪዎች “ የተወሰኑ የሲዳማ ኤጄቶ መሪዎች ዛሬ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ቀጥር ያለው ህዝብ ደማቅ አቀባበል ያደረገላቸው ሲሆን፤ በሀዋሳ አለም አቀፍ ስታዲዬም ለተገኝተው ህዝብን ኤጄቶዎቹ ምስጋና አቅርበዋል። በእስር ላይ በነበሩነት ወራት ከጎናቸው በመሆን ያበረታቷቸውን የቀድሞ ሲዳማ አመራሮችን አመስግነዋል። “ኤጄቶ የለወጥ ሃይል እንጂ አልቃይዳ ወይም አልሸባብ አይደለም” ብለዋል። አክለውም ለዶክተር አብይ አህመድ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ የአሁኑ የሲዳማ ዞን አስተዳደር የስልጣን ርክክቡን እንዲያፋጥኑ አሳስበዋል።

ሀዋሳ ከተማ ያለ ሀዋሳ ሀይቅ ማሰብ ከባድ ነው።

የሲዳማዋን ሀዋሳ ከተማ ያለ የፍቅር ሀይቋ ማሰብ በእርግጥም ከባድ ነው። የሲዳማ ክልል አስተዳደር እና የከተማዋ ነዋሪዎች በሀይቁ ላይ የተጋረጠውን አደጋ ለመቅረፍ በአንድነት መስራት ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም!!  

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ዛሬ በደረሰው የአፈር መደርመስ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ዛሬ በደረሰው የአፈር መደርመስ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡ በድንጋይ ካባ ላይ በደረሰ የአፈር መደርመስ በስራ ላይ የነበሩ የ 2 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ 3 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሀዌላ ቱላ ክፍለከተማ በሀዌላ ወንዶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኩዌ እየተባለ በሚጠራው የድንጋይ ካባ ላይ በደረሰ የአፈር ናዳ አደጋው መከሰቱን የገለፁት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ሮዳሞ ኪአ አደጋው በደረሰበት ሰዓት በስራ ላይ የነበሩ 5 ሰራተኞች ላይ ካባው ተንዶ 2ቱ ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ በ3ቱ ላይ ጉዳት ደርሶ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ገልፀዋል፡፡ አቶ ጥራቱ በየነ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ በተፈጠረው ድንገተኛ የአፈር መደርመስ ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው ከተማ አስተዳደሩ የጉዳቱን መጠን ለመቀነስ ጥረት እያደረገ ይገኛልም ብለዋል፡፡ መንግስት ተመሳሳይ ችግር ዳግም እንዳይከሰት የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ያመላከቱት ም/ከንቲባው በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ ምንጩ: የከተማዋ አስተዳደር 

የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና

በሀላሌ ሲዳማ የሲዳማ ብሔር አሁን በሚኖርበት አካባቢ የሰፈረው በ16ኛው ክፍለ ዘመን እንደነበረ የተለያዩ ጸሐፊዎች ያነሳሉ (Brogger 1986፣ 26፣ Hamer 1987፣ Braukamper 1977, Haileyesus Seba 2003)። የሲዳማ ብሔር በዚህ አካባቢ ከሠፈረበት ጊዜ ጀምሮ በአካባቢው ከነበሩ ሌሎች ማኅበረሰቦች ጋር መልካም ግንኙነት ነበረው። ሆኖም በ17ኛው ክፍለ ዘመን የራሱን የአስተዳደርና የአምልኮ ሥርዓት ለማከናወን በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም፣ በአከባቢው ይኖሩ የነበሩ ማኅበረሰቦች አዎንታዊ ምላሽ ባለመስጠታቸው ምክንያት ወደ ትግል ሊገባ ተገልዷል። ባደረገው ትግልም በአሸናፊነት በመውጣት የራሱን የአስተዳደር ሥርዓት መመሥረቱ ይነገራል (ቤታና ሆጤሳ 2013፣ 63)። በዚያን ጊዜ በትግሉ ግንባር ቀደም ነን ያሉና ትውልዳቸውን ከቡሼ የዘር ሐረግ የሚመዙት የሼቤዲኖ፣ ያናሴ፣ ዊጋ፣ ማልጋ፣ ሆሎ፣ ጋርብቾና ሃርቤጎና ጎሳዎች “የመሬቾ” የተባለና በአንጋ (Anga) የመንፃት (Wolapho) ፍልስፍና የሚመራ የባህል፣ የሃይማኖትና የአስተዳደር ሥርዓት እንደ መሠረቱ ይነገራል (Hamer 1987፣ 32)። በዚህ ሥርዓት ያልታቀፉ “የአለታ” ቡድን አባላት ይህን አደረጃጀት ተቃውመው የተሠለፉ ሲሆን፣ በሁለቱም ቡድን ያልተሳተፉ ሌሎች የሲዳማ ጎሳዎች በሦስተኛ ቡድንነት በመፈረጃቸው ምክንያት፣ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በሲዳማ ውስጥ የሦስት ቡድኖች ክፍፍል እንደ ተመሠረተ ይነገራል። የየመሬቾ ኃይል በሲዳማ ውስጥ የባህል፣ የሃይማኖትና የአስተዳደር ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ሚና የነበረው ቢሆንም በአለታ ቡድን ሊሸነፍ ችሏል። ይህም ለሁለቱም ቡድኖች መፍረስና በፍልስፍናው ስም ለሚጠራ የወላዊቾ (Wolawichcho) ቡድን መመሥረት ምክንያት በመሆን የኃይል አሠላለፉን ከሦስት ወ

Honey Producers Cooperative at Sidama Shebedino

በ62 ሚሊየን ዶላር ወጩ በሀዋሳ የሚገነባው የሂልተን ሪዞርት ሆቴል ሙሉበሙሉ ወደ ግንባታ ሊገባ መሆኑን ገለፀ

በ62 ሚሊየን ዶላር ወጩ በሀዋሳ የሚገነባው የሂልተን ሪዞርት ሆቴል ሙሉበሙሉ ወደ ግንባታ ሊገባ መሆኑን ገለፀ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እና የደቡብ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርዕስቱ ይርዳው እና ሌሎች የስራ አመራሮች በሀዋሳ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል፡፡ የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻን መነሻ በማድረግ የሚገነባው ይህ ባለ አምስት ኮኮብ የሂልተን ሪዞርት ሆቴል አጠቃላይ እንቅስቃሴ የጉብኝቱ አንድ አካል ነበር፡፡ ሆቴሉ በ62 ሚሊየን ዶላር ወጪ አለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ የሚሳረ ሲሆን 20 የውጭ ሀገር ዲዛይነሮች የተሳተፉበት እና 2.8 ሚሊየን ዶላር የፈጀ የግንባታ ዲዛይን ስራው ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ወደ ግንባታ ስራ ሊገባ መሆኑን የሆቴሉ ባለቤት አቶ ሳሙኤል ታፈሰ ገልፀዋ፡፡ ሪዞርቱ 150 ደረጃቸውን የጠበቁ መኝታ ክፍሎች አለም አቀፍ ዝግጅቶችን ማስኬድ የሚችሉ የመሰብሰቢያ አዳራሾች 6 ተጓዳኝ ህንፃዎች እንደሚኖሩትም አቶ ሳሙኤል ገልፀዋል፡፡ የህንፃ ግንባታ ስራው በራሱ በሰንሻይን ኮንስትራክሽን የሚሰራ ሲሆን የማጠቃለያ (የፊኒሺንግ) ስራውን ደግሞ ከፈረንሳይ፣ ከቻይና ከዱባይ እና ከሌሎች የዓለም ሀገራት ባለሞያዎች የሚሳተፉበት እንደሆነም ነው አቶ ሳሙኤል የገለፁት፡፡ አቶ ርዕስቱ ይርዳው የቡብ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳደር ይህ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርት ሆቴል በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲጋባ በግንባታው ወቅትና በሆቴል ዘርፍ ከሚፈጥረው የስራ ዕድል በተጨማሪ ለሀዋሳ ከተማም ሆነ አጠቃላይ እንደሀገር የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴውን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚስኬድ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ሆቴሉ በግንባታው ወቅት ብቻ ለ1500 ሰዎች የስራ ዕ

የኖቭል ኮሮና ቫይረስ እንዳይከሰት አስቀድሞ የመከላከል ስራው ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ

የኖቭል ኮሮና ቫይረስ እንዳይከሰት አስቀድሞ የመከላከል ስራው ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ከኢትዮጵያ ማህበረሰብ ጤና ኢንስቲቲውትና ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ለከተማው የስራ አመራር እና ለጤና ባለሞያዎች በኖቭል ኮሮና ቫይረስ ምንነት፣ መንስኤዎች፣ ምልክቶችና የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በስልጠናው ወቅት ወደ ሀዋሳ የገቡ 14 ቻይናውያን በኖቭል ኮሮና ቫይረስ መያዝ አለመያዛቸውን ለማረጋገጥ የቅርብ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡ ስልጠናው በተሰጠበት ወቅት በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ የሚሰሩ 14 የሚጠጉ ቻይናውያን ከቻይና ወደ ሀዋሳ መግባታቸውን ተከትሎ ከተማ አስተዳደሩ በበሽታው መያዝ አለመያዛቸውን ለማረጋገጥ በአንድ አካባቢ በማቆየት የቅርብ ክትትል እያደረገላቸው መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ቡሪሶ ቡላሾ ገልፀዋል፡፡ 14ቱ ቻይናውያን በሽታው ከተስፋፋባቸው ከሁቤይ ግዛት ከውሀን ከተማ የመጡ አለመሆኑን እና የሙቀት እና ሌሎች የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች ምርመራ ተደርጎላቸው ነፃ መሆናቸው ቢታወቅም ለተጨማሪ 14 ቀናት ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚቆዩም አቶ ቡሪሶ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የሀገራችንም ሆነ የከተማችን ነባራዊ ሁኔታ መከላከል ላይ ቅድሚያ ሰጥተን እንድንሰራ አስገዳጅ መሆኑን ስልጠናውን ከሰጡት መካከል ከኢትዮጵያ ማህበረሰብ ጤና ኢንስቲቲውት የመጡት ዶክተር ዮሴፍ አስራት ናቸው፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሙ የአመራሩን እና የጤና ባለሞያውን ግንዛቤ በማስፋት አስቀድሞ ለመከላከልም ሆነ በአንድ አጋጣሚ በሽታው ቢከሰት ምን አይነት እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ እ

የሲዳማ ብሔር ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ቀን የሚከበርባቸውን አካባቢዎች የማፅዳት ስራ በሀዋሳ ከተማ ተጀመረ

የሲዳማ ብሔር ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ቀን የሚከበርባቸውን አካባቢዎች የማፅዳት ስራ በሀዋሳ ከተማ ተጀመረ፡፡ የሲዳማ ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ቀንን ምክንያት በማድረግ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በዓሉ በታላቅ ድምቀት ከሚከበርበት ከአዲሱ ኢንተርናሽናል ስታዲየም መነሻውን ያደረገ የስታዲየሙን ዙሪያ እንዲሁም የከተማ ማፅዳት ስራ መጀመሩን አቶ ዘሪሁን ሰለሞን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ ገልፀዋል፡፡ የሲዳማ ብሔር እራሱን በራሱ ለማስተዳደር ህዝበ ውሳኔ በማካሄድ በነፃ ፍቃዱ ህገ-መንግስታዊ መብት መጎናፀፉን ተከትሎ የአዲሱ የሲዳማ ክልል ምስረታ እና የስልጣን ርክክብ ስራ በመከናወን ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ዘሪሁን የስልጣን ርክክብ ስራው ሲጠናቀቅ ታላቅ ህዝባዊ የደስታ መግለጫ ፕሮግራም እንደሚኖርም አስታው ሰዋል፡፡ ለአዲሱ ክልል ምስረታ እና ለስልጣን ርክክብ ስራ ከተዋቀረው ኮሚቴ አንዱ በሆነው የቦታ መረጣ እና ዝግጅት አስተባባሪ ኮሚቴ አማካኝነት ዛሬ የተጀመረው የፅዳት ስራ ሀዋሳ ከተማ ወትሮም የምትታወቅበትን ውብ፣ፅዱ አረንጓዴ እና ምቹ ከተማነቷን በማስቀጠል በዓሉ በሚከበርበት ዕለት መላው የደስታው ባለቤት እና ተካፋይ ህዝብ እንዲሁም እንግዶችን ማራኪ በሆነ መንገድ ለማስተናገድ ከሚያስችሉ የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ውስጥ አንዱ መሆኑን ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ Source

29 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ የጫነ አንድ ተሸከርካሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ገልፀ

29 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ የጫነ አንድ ተሸከርካሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ገልፀ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ እንዲሁም ኮማንደር ኢዮብ አቤቶ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም መሰረት ትላንት ምሽት 5፡00 አካባቢ ኮድ 3/ 34480 አ.አ ታርጋ ቁጥር በለጠፈ አይሱዙ ኤፍ.ኤስ.አር ተሸከርካሪ 29 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ በመኪናው ከፋብሪካ ውጭ በተሰራ በቀላሉ የማይገኝ ሚስጥራዊ ቦታ ተደብቆ ሲጓዝ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልፀዋል፡፡ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያውን ሲያጓጉዙ የነበሩት የመኪናው አሽከርካሪ፣ የህገ-ወጥ ጦር መሳሪያው ባለቤት እና የመኪናው እረዳት በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ተገልጿል፡፡ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር መረጃው ከሳምንት በፊት አስቀድሞ በደረሰ ጥቆማ የታወቀ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ብቃት ያለቸውን የፖሊስ አመራሮች በመመደብ ጉዳዩ በሚስጥር ሲጣራ ቆይቶ ትላንት ምሽት በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው፡፡ የጦር መሳሪያው ከየት ተነስቶ ወደየት እንደሚሄድ ለምን ዓላማ ሊውል እንደተፈለገ ጭምር መረጃዎች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን ጉዳዩ በምርመራ ሂደት ላይ በመሆኑ ሳይገለፅ ቀርቷል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ ሀይሉን አቅም በማጠናከር እና ከህዝብ ጋር በመቀናጀት ማንኛውንም አይነት ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ሮዳሞ ኪአ ገልፀዋል፡፡ በዚህም የከተማዋ ሰላም እና የፀጥታ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እየተጠናከረ መምጣቱን ኮለኔል ሮዳሞ ገልፀው

Angry workers spurn Ethiopia's 'industrial revolution'

Hawassa (Ethiopia) (AFP) Zemen Zerihun thought he'd left farming behind and found the ticket to a better life when he began a job cutting fabric for a clothing company at a massive industrial park in southern Ethiopia. But the 22-year-old ended up quitting within months, weary of working eight hours a day, six days a week and still not making ends meet earning $35 a month. Managers were so strict they would go into bathrooms and yank out workers deemed to be taking too long, he said. His supervisor would loudly berate him as "slow" and "lazy" when he failed to keep pace on the production line, he told AFP. "After I joined the company, I suffered," he said. "The supervisors treat you like animals." Experiences like his highlight a major challenge facing Ethiopia's push to embrace industrialisation and become less dependant on agriculture. By attracting foreign investors through cheap labour, it wants to follow the mod