Skip to main content

ኤጄቲማ ፌደራሊስት ፓርቲ- EFP ጊዜያዊ አስተባባሪዎች የተሰጠ መግለጫ


ከጊዜያዊ አስተባባሪዎች የተሰጠ መግለጫ
የሲዳማ ህዝብ ላለፉት 130 ዓመታት ለብሄር ብሄረሰቦች እራስን በራስ የማስተዳደር መብትና ለሉኣላዊ የስልጣን ባለቤትነት እውን መሆን መራራ ትግል ሲያደርግ እንደቆየ ይታወቃል።
አሁን ላይ ለረጅም ግዜ ሲደረግ የነበረው ትግል ወደ ወሳኝ የድል ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተገኘውን ድል ጠብቆና አድምቆ ለመሄድ የተደራጀና ህዝባዊ መሰረት ያለው ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው። ሆኖም አሁን ያለው አከባቢያዊና ሀገራዊ የፖለቲካ እውነታ ህዝባችን እና ያገኘውን ድል የሚመጥን ከመሆን በተቃራኒ ህዝባችን በጠየቀው ጥያቄ እንዲሸማቀቅና ጥፋተኝነት እንዲሰማው በማድረግ ከፍተኛ የሆነ የብቀላ ወጥመድ እየተዘረጋ ያለበትን ሁኔታ አስተውለናል። ህዝባችንን ዳግም በጨለማ ለመወርወር እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች ከግዜ ወደ ግዜ መልካቸውንና መጠናቸውን እየቀየሩ በህዝባችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የሞራል እና የስነ ልቦና ጫናዎችን እየፈጠሩ ቆይተዋል። ለአብነትም የሲዳማ ህዝብ ብዙ ዋጋ ከፍሎ ያገኘው በክልል የመደራጀት መብት የስልጣን ርክክብ እንዳይደረግና እንዲዘገይ ከዛም ባሻገር ከህዝባችን ፍላጎትና ውሳኔ ውጪ የሆነ ፖለቲካዊ መዋቅር ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ሙከራ የዚህ ሴራ ማሳያ ነው። ከዚህም ባለፈ ህዝባችን ድል ሊያስጠብቅ የሚችለውን ህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊና ህገ መንግስታዊ ስርዓትን አጠልሽቶ ለማሰናከል እየተደረገ ያለው ጥረት ይህ ነው የሚባል አይደለም።
ለዚህ ሴራ ትግበራ ይሆን ዘንድ የሲዳማ ፖለቲካ ሊህቃኖችን፥አክቲቪስቶችን እና ጋዜጠኞች ላለፉት 7 ወራት ያለ ፍርድ በእስር እንዲሰቃዩ ተደርጎ የሚመሰረተውን የሲዳማ ክልል አቅም አልባና ደካማ አድርጎ ለማቅረብ የተኬደው ርቀት ከፍተኛ ነው። በህዝባችን ላይ እየተካሄደ ያለው ይህ ሁሉ የብቀላ ዘመቻ "ምን ያመጣሉ" ከሚል ስሜት የመነጨ የንቀት ዱላ መሆኑን ተገንዝበናል።
ይህ በመሬት ላይ ያለው እውነታና በቀጣይነት የሚኖረው የህዝባችን እጣ ፈንታ ባሳሰባቸው የሲዳማ ምሁራን አነሳሽነት(አስተባባሪነት) የተጠነሰሰው ኤጄቲማ ፌደራሊስት ፓርቲ በርካታ ስራዎችን በውስጥ ሲሰራ ቆይቶ ከብዙ አይነት ዛቻዎችና የማጥቆር ፕሮፓጋንዳዎች አልፎ ዛሬ ወደ ወሳኝ ተቋማዊ ደረጃ ተሸጋግሯል። ፓርቲው በአስር አስተባባሪ( አነሳሽ ) ወገኖች የተጀመረ ሲሆን በቅርቡ የአባላት ምዝገባውን አጠናቆ መስራች ጉባኤ በመጥራት በይፋ ይመሰረታል። በዚህም ጉባኤ ከፓርቲ ስያሜ፣ ከፖለቲካ ርዕዮት፣ ከፓርቲ አመራሮችና መሰል ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች እልባት ያገኛሉ። ፓርቲው እንደ አስፈላጊነቱ ከተለያዩ አካላት ( ፓሪቲዎች ) ጋር በፎረም፣ በቅንጅት አልያም በግንባር ሊሰራ የሚችልባቸው ሁኔታዎች የተጠበቁ ሲሆን ተራማጅ ፌደራሊስታዊ አቅጣጫን የሚከተል መሆኑን ሁሉም ሊያወቀው ይገባል እንላለን።
ከጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ
ጥር 21/2012 ሲዳማ፣ ሀዋሳ፣ ኢትዮጵያ

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa