Skip to main content

ለሶስተኛ ዙር የልማት ተነሺዎች ምትክ ቦታ በእጣ የማስተላለፍ ስራ ተከናወነ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በአካባቢ የልማት ጥናት መሰረት በዩኤልዲፒ የልማት ስራ ለሁለት ዙር ተነሺዎች ምትክ ቦታ በእጣ የማስተላለፍ ስራ እንደተሰራ ይታወቃል፡፡
በዛሬው እለትም ለሶስተኛ ዙር በታቦር ክ/ከተማ ፋራ ቀበሌ በመንገድ ልማት ተነሺ ለሆኑ 122 ነባር ባለይዞታዎች በዶሮ እርባታ አካባቢ በተዘጋጀ መሬት እንደየ መሬት ይዞታቸው በዕጣ በመለየት ምትክ ቦታ የማስተላፉ ስራ ተከናወኗል፡፡
እስከ አሁን ለ240 ነባር ባለይዞታ አርሶ አደሮች ምትክ ቦታ የተሰጣቸው ሲሆን በአጠቃላይ 1136 ተነሺዎችን ከሁለት ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በተዘጋጀላቸው ቦታ በማሳረፍ ሙሉ በሙሉ የመንገድ ከፈታ ስራዎችን በመስራት የህብረተቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ከተማ አስተዳደሩ እየሰራ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል፡፡
አቶ ጥራቱ ከዚህ ቀደም በተላለፉ ቦታዎች አካባቢ የተከናወኑ ተግባራትን በስፍራው ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ልማቱን ሊያፋጥኑ የሚችሉ አሰራሮች እንደሚተገበሩም ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ በጎርፍ ምክንያት የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ በዋርካ ሆቴል እና በሳውዝ ስታር አካባቢ የተጀመሩ የጎርፍ ውሃ መውረጃ ቦዮች በተፈለገው ፍጥነት ያልተጓዘ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባ አቶ ጥራቱ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ህብረተሰቡ መታገስ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ የሀዌላ ቱላ ክ/ከተማን ጨምሮ የመንገድ፣ የመብራት፣የውሃ፣ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም፣ የጎዳና ልጆችን በማሰልጠን እና ሌሎች መልካም አስተዳደር እና የልማት ስራዎች ላይ ከተማ አስተዳደሩ በየደረጃው ለማከናወን በበጀት ተደግፎ ተግባራት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
በመንግስት ተቋማት ውስጥ ያሉ ብልሹ አሰራሮችን ለማስወገድም የተለያዩ ማስተካከያዎች መደረጉን የተናገሩት አቶ ጥራቱ ከዚህ ባለፈም ችግር ያለባቸው አካላትን በህግ የማስጠየቅ ስራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡
በእጣ የማውጣት ስፍራ ከተገኙ የልማት ተነሺዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደተናገሩት አሁን እየተከናወነ ያለው ተግባር የረጅም ዓመታት ጥያቄ ከመሆኑም በላይ በመንገድ፣በውሃ እና ለእለት ተእለት ማህበራዊ ግንኙነት ጭምር ትልቅ ተግዳሮት እንደነበረ አስታውሰው ከተማ አስተዳደሩ የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ሲጠይቁ ለተጀመረው የልማት ስራ አጋዥ እንደሚሆኑ በመግለጽ ነው፡፡


Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa