Skip to main content

መቀመጫውን በሀዋሳ ከተማ ያደረገው ኢፓርኬ የሁለንተናዊ ብቃት ማበልጸጊያና የስልጠና ማዕከል በራዕይና በእይታ ቅኝት ዙሪያ የማነቃቂያ ስልጠና ሰጠ

መቀመጫውን በሀዋሳ ከተማ ያደረገው ኢፓርኬ የሁለንተናዊ ብቃት ማበልጸጊያና የስልጠና ማዕከል በራዕይና በእይታ ቅኝት ዙሪያ የማነቃቂያ ስልጠና ሰጠ፡፡
በ 3 ዋና ዋና አርዕስቶች ማለትም፤በራዕይና በራዕይ ተግዳሮቶች፡ በአላማ ጽናት እንዲሁም በዕይታ ቅኝት ዙሪያ በተሰጠው ስልጠና ላይ በከተማው በተለያዩ ተቋማት በመሪነት ላይ የሚገኙ ግለሰቦች፤ ወጣት ነጋዴዎች እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡
የኢፓርኬ ስልጠና ማዕከል መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አራርሶ ገረመው እንደገለጹት ስልጠናው አላማና ራዕይ ያለውን ዜጋ ከማብቃት ባለፈ ወጣቶች በነገሮች ሳይሰናከሉ አርቀውና አስፍተው ማየት እንዲችሉ፤ ብቃታቸውን ማሳደግ እንዲችሉ፤ ስለ ሀገርና ዜጋ ማሰብ እንዲችሉ፤ ውስጣዊ አቅማቸውን ተጠቅመው አላማቸውን ማሳካት እንዲችሉ እንዲሁም ህይወታቸውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ ከማገዝ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳና የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ከተማ ዶባ በበኩላቸው ወጣቱን ማዕከል ባደረገው የከተማው ሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴ ላይ መሰል ስልጠናዎች የሚኖራቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይህንንም መሰረት በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ ከኢፓርኬና መሰል ተግባራት ላይ ከተሰማሩ ድርጅቶች ጎን በመቆም ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ከተማ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የሀዋሳ ከተማ ህዝብ ግንኙነት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መልካሙ ተፈራ በበኩላቸው ወጣቱን መሰረት ያደረጉ የኢፓርኬን አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች በማድነቅ በበኩላቸው ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን አሳውቀዋል፡፡ አክለውም ወጣቶችና ሌሎች የስልጠናው ተካፋዮች ከስልጠናው ያገኙትን ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር ከራስ አልፈው ሀገርንና ወገንን ለመጥቀም ቁርጠኛ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡
በዕለቱ ከቀረቡት የስልጠና ርዕሶች መሀል “የራዕይ ተግዳሮቶች” በሚል በደራሲ ስመጥሩ ታየ የቀረበው የሚገኝበት ሲሆን “በአላማ ጽናት” ዙሪያም ከሀገረ አሜሪካ የመጡት ምሁር አቶ ታደለ ነጋሽ ሰፊ ትንታኔ በመስጠት ጠቃሚ ዕውቀቶችን ለሰልጣኞች አስተላልፈዋል፡፡
የስልጠናው ዋነኛ አካል የሆነው አርዕስት በአቶ አራርሶ ገረመው የቀረበው “የእይታ ቅኝት” ሲሆን አላማን መኖር፤ እይታን ማስተካከል፤ ቦታን ማወቅ፤ ውስጣዊ አቅምን ማዳበርና በመሳሰሉት የስኬት ቁልፍ ሚስጥሮች ዙሪያ ሰፊ ትንተናን አካቷል፡፡
በቀጣይም ኢፓርኬ መሰል ተግባራቶችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa