Skip to main content

ከሲዳማ ኤጄቶ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ


የሲዳማ ህዝብ ለዘመናት ባደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል እና በከፈለው ውድ መስዋትነት ፍሬ እራስን በእራስ የማስተዳደር መብቱን በህዳር 10/2012 ዓ.ም በተካሄደው እና ከ2.3 ሚልዮን በላይ መራጮች ተሳትፈውበት ከ98/100 በላይ ይሁንታን በሰጡበት ህዝበ-ውሳኔ አማካኝነት በድል ማጠናቀቁ ይታወቃል። ምንም እንኳን ለዚህ ጣፋጭ ድል ለመብቃት ያሳለፈነው ጉዞ እጅግ መራራ ቢሆንም ክብር እና ምስጋና በትግሉ ወቅት ለተሰዉ ታጋይ ሰማዕታት ይሁንና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣውን የአደራ እዳ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲቋጭ አድርገናል።
በህዝቡ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና ህገመንግስቱን ተከትሎ ጥያቄውን ለማስመለስ ሲያካሂድ በነበረው ሰላማዊ የትግል አካሄድ ላይ በመንግስት በኩል በተፈጸመ ኢ-ህገመንግስታዊ የፖለቲካዊ ደባ ምክንያት ከ140 የሚልቁ ንጽሀን የሲዳማ ተወላጆች ህይወት መቀጠፉ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። "ለህገመንግስታዊ ጥያቄያችን ህገመንግስታዊ ምላሽ ብቻ እናሻለን" በሚል መርህ ሲካሄድ በነበረው ሰላማዊ ትግል ወቅት ላይ ከህገመንግስቱ ድንጋጌ እና አካሄድ ውጪ በሆነ መልኩ ከመንግስት በኩል የቀረቡ አማራጭ የፖለቲካ ውሳኔዎችን አምርረን መቃወማችን ይታወሳል።
ይሁንና ህዝቡ ባደረገው ተቃውሞ እና በከፈለው መስዋትነት የብሄሩ እራስን በእራስ የማስተዳደር ጥያቄ ህገመንግስቱ በምያዘው መልኩ ከሁለት ወራት በፊት በተካሄደው ህዝበ-ውሳኔ ክልል ለመሆን የሚያስችለንን ድምጽ በማግኘት ያጠናቀቅን ቢሆንም የህዝበ-ውሳኔው ውጤት ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ በደቡብ ክልል መንግስት እና በሲዳማ ክልል መካከል መደረግ የነበረበት የስልጣን ርክክብ ሳይካሄድ ቆይቷል።ህዝቡ ይህን የመንግስት ዝግመታዊ የሴራ አካሄድ በጥርጣሬ በመመልከት ባስቸኳይ የስልጣን ርክክቡ እንዲካሄድ በሲዳማ ተወካዮች ላይ እና በሚመለከተው አካል ላይ ከፍተኛ ጫና ሲያሳድር የከረመ ሲሆን እስከ ጥር 30 ድረስ የስልጣን እርክክቡ ተጠናቆ የክልል ምስረታ ስነ-ስርዓት እንደሚደረግ የተገባለትን ቃል በታላቅ ጉጉት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ከዚህ ውሳኔ ውጪ አሁን በተለያዩ አካላት በኩል የሲዳማን ህዝብ እራስን በእራስ የማስተዳደር መብት ለመጋፋት እና በህገመንግስቱ መሰረት ምላሽ አግኝቶ የተቋጨን ጥያቄ በፖለቲካ ውሳኔ ወደ ኋላ ለመቀልበስ የሚደረጉ ሙከራዎች ሁሉ ካለፉ ስህተቶች ያለመማር እና አሁንም አላስፈላጊ የህዝብ ደም ለማፍሰስ የሚደረግ አደገኛ አካሄድ እንደሆነ አድርገን እንወስደዋለን፡፡የሲዳማን ህዝብ የዘመናት ጥያቄ ለማስመለስ ቆርጦ የተነሳው ይህ የመጨረሻው ትውልድ(ኤጄቶ) እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ አሁንም መርህ አልባ የሆኑ ፖለቲካዊ አጀንዳዎችን በጽናት የሚታገል መሆኑንና በደም የተገኘውን የህዝባችንን ሉአላዊ የስልጣን ባለቤትነት ለድርድር የማያቀርብ መሆኑን ሁሉም ጠንቅቆ እንዲገነዝብ እንፈልጋለን።
ሀዋሳ ሲዳማ ኢትዮጵያ🇪🇹
#ኤጄቶ

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa