Skip to main content

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስረታ በአጭር ጊዜ ውስጥ አውን ማድረግ የሚያስችል ስራ እየተከናወነ ይገኛል

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስረታ በአጭር ጊዜ ውስጥ አውን ማድረግ የሚያስችል ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ለምዕተ አመትና ከዚያ በላይ የሲዳማ ብሔር ለመብቱ እና ነጻነቱ የህይወት እና አካላዊ መስዋዕትነትን በመክፈል ትግል ማድረጉ የሚታወቅ ነው፡፡
በዚህም ጥቂት የማይባሉ የብሔሩ ተወላጆች ከአጼው ዘመን ጀምሮ እስከ ኢህአዲግ አገዛዝ ድረስ በተደራጀ እና ባልተደራጀ መልኩ ኢፍትሀዊነትን እና አንባገነንነትን በመታገል ጭምር የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት ችለዋል፡፡
ይህ ከሀገር አልፎ በጎረቤት ሀገር ሞቃዲሾ ሳይቀር ወታደራዊ ትግልን በተደራጀ መልኩ በማድረግ ጭምር አስፈላጊውን የነጻነት ታጋዮችን በማጠናከር ትግሉን ያለማቋርጥ ያደረገው የሲዳማ ብሔር ዛሬ ላይ የታየውን ድል ለመጎናጸፍ ያላሰለሰ ጥረቱ ሆኖም ይገኛል፡፡
ከዚህ ጎን ለጎንም የብሔሩ ምሁራን እና አክቲቪስቶች በተመሳሳይ መልኩ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የፖለቲካዊ የዲፕሎማሲ አማራጮችንም ሆነ ነጻ የሆኑ ትግሎችን በማቀጣጠል የበኩላቸውን መወጣት ችለዋል፡፡
በዚህ አይነት መልኩ ከዳር ይደርስ ዘንድ ዋጋ የተከፈለበት ይህ የብሔራችን ትግል በርካቶች መስዋዕት የሆኑበት እና በርካቶች ደግሞ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ማቅ እስከመልበስ ያላሰለሰ ጥረት ያደረጉበት እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል፡፡
ለሀገራችን ጭምር አዲስ የትግል እሳቤን በማከል እንዲሁም ለህብረ ብሔራዊ ፌድራላዊ ስርዓታችን መጎልበት አዲስ ምዕራፍ እስከመሆን በደረሰ መልኩ ህዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም ነጻ፣ ፍትሀዊ እና ሁሉን አቀፍ የሆነ ህዝበ ውሳኔን ማረጋገጥ ያስቻለ ምርጫ ማካሄዳችን ይታወቃል፡፡
በዚህም መላው የሀገራችን ህዝቦች፣ ታላላቅ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ሚዲያዎች ሳይቀሩ በግልጽ እውቅና የቸሩት የምርጫ ሂደት እና ውጤትን እውን ማድረግ ያስቻለ ጨዋ አሰራር እና ከጨዋ ህዝብ እና ማንነት የሚጠበቅ ተግባርን እውን ማድረግ ችለናል፡፡
ይህን ተከትሎ ግን ላለፈው አንድ ወር የብሔራዊ ክልላችንን ምስረታ በይፋ እውን መሆን አንዳንድ የውስጥ እና የውጭ አሰራሮችን ከማስተካከል አንጻር መጓተቶች መኖራቸውን ተከትሎ በብዙዎቻችሁ ዘንድ ጥያቄ እየሆነ ሲንጸባረቅም ማየት ችለናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በይፋ 10ኛው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትም ሆኖ የሲዳማን ብሔር በፌድራላዊ መዋቅራችን አንዱ ማንነት በመሆን እውን የሚያደርገው አደረጃጀትን አስመልክቶ ከደቡብ ክልል ጋር አስፈላጊውን ሁሉ በማከናወን እና ለዚሁ ስኬት አስፈላጊ የሆኑ የኮሚቴ መማክርቶችን በማዋቀር ተገቢው እንቅስቃሴ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ይህ በተለያየ ዘርፍ እና ተልዕኮ ተዋቅሮ ለክልላዊ አደረጃጀቱ ይፋ መሆን እየተንቀሳቀሰ ያለው የኮሚቴ መማክርት አሁን ባለው ፍጥነት እና ትጋት በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጨባጭ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትን በርክክቡ እውን የሚያደርግ እንደሚሆን ይታመናል፡፡
ይህ በብርቱ የሲዳማ ልጆች ትግል እና በለውጡ መሪ ምላሽ ያገኘው የዘመናት ጥያቄ ትግሉን የሚመጥን ዝግጅት ስለምፈልግ በእለቱም ከሀር ውስጥ እና ከባህር ማዶ ታላላቅ የሀገር መሪዎች፣ ዲፖሎማቶች እና ታዋቂ ግለሰቦች እና ምሁራን እንደሚገኙ ያለው መርሀ ግብር ያስረዳል፡፡
በመሆኑም መላው ህዝባችን በተደራጀ መልኩ ለክልሉ ምስረታ ይፋ መሆን እየተከናወነ ያለውን ተግባር እና ተልዕኮ በመገንዘብ ከመወዲሁ ዝግጁ በመሆን ክልላችንን በጋራ እንመስርት ለማለት እንወዳለን፡፡
ምንጭ፤ የከተማዋው አስተዳደር ነው 

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa