Skip to main content

የከተማዋን ደህንነት በማስጠበቅ ህብረተሰቡን በእኩል መልኩ ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀታቸውን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አባላት ገለጹ

የከተማዋን ደህንነት በማስጠበቅ ህብረተሰቡን በእኩል መልኩ ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀታቸውን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አባላት ገለጹ፡፡
አባላቱ ይህንን የገለጹት ለሶስት ቀናት ባካሄዱት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው፡፡
ሰራዊቱ ባሳለፈው የስራ ጊዜያት ውስጥ የነበረ ቡድንተኝነት የስራ ሞራላቸውን የነካ እንደሆነ ገልጸው አሁን እየተፈጠረ ባለው ግልጸኝነት እጅግ መደሰታቸውን ሲናገሩ ህብረተሰቡን በቁርጠኝነት ለማገልገል ምንም አይነት እንቅፋት እንደማኖር በመተማመን ነው፡፡
በአንዳንድ አባላት በሚስተዋሉ የስነ ምግባር ችግሮች በህብረተሰቡ ዘንድ አሜኔታ እንድናጣ ሆነናል ያሉት አባላቱ ውስጣዊ ችግሮቻችንን የሚፈታ አመራር በማግኘታችን የስራ ሞራላችን ከፍ ብሏልም ብለዋል፡፡
የሰራዊት አባላቱ አክለውም ህግን ከማክበርና ከማስከበር አንጻር ትኩረት ሰጥተው ለመስራትና ህብረተሰቡን ለመካስም ጭምር መዘጋጀታቸውን ነው የተናገሩት፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት ባለፈው የሪፍረንደም ወቅት እና የገብርኤል መንፈሳዊ በዓል በሰላም መጠናቀቅ የሰራዊቱ ሚና ከፍተኛ እንደነበር የተናገሩት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ናቸው፡፡
አቶ ጥራቱ አክለውም አንዳንድ የሰራዊቱ አባላት ህብረተሰቡን በእኩል ከማገልገል አንጻር፣ በጥቅማ ጥቅም መደለል፣ቡድንተኛ መሆን፣ሙያዊ ስነምግባርን በመዘንጋት እና በሌሎች ምክንያቶች ኃላፊነታቸውን እንዳልተወጡ በግምገመው ወቅት የተለዩ ችግሮች እንደነበር አንስተዋል፡፡
በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተቀመጠለት አሰራር እየገመገመ እርምጃ ከመውሰድ አኳያ የፖሊስ ማኔጅመንቱ ጉድለት እንዳለበትም ከንቲባው ተናግረዋል፡፡
የሰራዊቱ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው የተለያዩ አልባሳትና ቁሳቁስ ውስንነት ችግርን ለመፍታት 14 ሚሊዮን ብር በመመደብ ግዥ መፈጸሙን የገለጹት ከንቲባው ከዚሁ የመብት ጥያቄ ጎን ለጎን የአመለካከት ለውጥ በማምጣት የስራ ድስፒሊንና ሞራልን በማጣመር ሙያዊ ግዴታን መወጣት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
የአዲሱ ክልል ምስረታ በቅርብ ጊዜ እንደሚከናወን የገለጹት አቶ ጥራቱ ወደ ከተማዋ የሚመጣውን የኢንቨስትመንት እና የቱሪስት ፍሰት በአግባቡ ለመጠቀም ሰራዊቱ ትልቅ ኃላፊነት አለበትም ብለዋል፡፡
ከሰራዊቱ ለቀረቡ የትምህርት እድል፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ የመኖሪያ ቤት እና ሌሎች ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡
በመድረኩም ባለፉት አራት ወራት የተሻለ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የፖሊስ አባላት፣ የትራፊክ ፖሊሶች፣ክ/ከተሞች በየደረጃው ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ሲሆን ልዩ የዋንጫ ተሸላሚዎች ዋንጫ ተቀብለው ለአባላቱ የተገዙ ቁሳቁሶችም ርክክብ ተደርጓል፡፡

ዜናው የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ግኙኝነት ነው 

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa