Skip to main content

በግል ቂም ተነሳስቶ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የዶርም አባሉን ህይወት ያጠፋው ተማሪ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ

በግል ቂም ተነሳስቶ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የዶርም አባሉን ህይወት ያጠፋው ተማሪ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ
ድርጊቱ በቀን 30/4/2012 ዓ.ም ትላንት ምሽት 4 ሰዓት አካባቢ የተፈፀመ መሆኑን የገለፁት ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ ናቸው፡፡
በሀዋሳ ዩኒቭርስቲ ተማሪ በሆኑ ሁለት ግለሰቦች መካከል በግል ፀብ በተፈጠረው በዚህ ግጭት የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆነው ግለሰብ ህይወት በስለት ተወግቶ ማለፉን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
ግጭቱ በተፈጠረ ሰዓት በአካባቢው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለፖሊስ ባደረጉት ጥሪ መሰረት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ደርሶ ጉዳት የደረሰበት ተማሪ በዩኒቨርስቲው ባለ ክሊኒክ የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ ያደረገ ቢሆንም ተጎጂው ሪፈር ተፅፎለት ወደ ሪፈራል ሆስፒታል ተልኮ የህክምና እርዳታ እያገኘ ባለበት ህይወቱ ማለፉን ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ እና በድርጊቱ የተሳተፉ አካላት በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው በተደረገው ምርመራ እና ማጣራት ወንጀሉ የተፈፀመው በሟች እና በገዳዩ መካከል በነበረ የቆየ ግጭት ምክንያት በተያዘ ቂም መሆኑን የገለፁት ኮለኔል ሮዳሞ ናቸው፡፡
በዚህ ድርጊት ባልተጠበቀ ሁኔታ የተማሪው ህይወት ከጠፋ ብኋላ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ ጥዋት ላይ ብቻ የመማር ማስተማር ሂደቱ መጠነኛ መስተጓጎል እንደገጠመው የገለፁት ኮለኔል ሮዳሞ በአሁን ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በሁሉም ካፓስ የመማር ማስተማር ስራው በሰላማዊ መንገድ የቀጠለ መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
በአሁን ሰዓት ከሁሉም የፀጥታ ሀይል የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት በሁሉም ካምፓሶች የተቋቋመ መሆኑን የገለፁት ኮለኔል ሮዳሞ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ምንም እንኳን ግጭቱ በግል ቂም በተፈጠረ ፀብ የተፈፀመ መሆኑ በምርመራ የተረጋገጠ ቢሆንም በማህበራዊ ሚዲያዎች የሁለቱን ተማሪዎች ግጭት የብሔር ካባ በማልበስ የሀሰት መረጃ የሚያሰራጩ አካላት መኖራቸውን ኃላፊው ገልፀው እነዚህ ኃላፊነት የጎደላቸው በጥቅም የታወሩ አካላት የሚያሰራጩት የሀሰት መረጃ ከእውነት የራቀ ሚዛናዊነት የጎደለው መሆኑን መላው ህብረተሰብ ሊገነዘበው እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በዚህ ባልተጠበቀ አጋጣሚ በጠፋው የተማሪ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን የገለፁት ኮለኔል ሮዳሞ ኪአ በከተማ አስተዳደሩ ስም ለሟች ቤተሰቦች፣ ዘመድ አዝማድና ወዳጆች መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡
\ዜናው የሀዋሳ ከተማ ህዝብ ግኙኝነት ነው

Comments

Popular Posts

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa