ከጊዜያዊ አስተባባሪዎች የተሰጠ መግለጫ የሲዳማ ህዝብ ላለፉት 130 ዓመታት ለብሄር ብሄረሰቦች እራስን በራስ የማስተዳደር መብትና ለሉኣላዊ የስልጣን ባለቤትነት እውን መሆን መራራ ትግል ሲያደርግ እንደቆየ ይታወቃል። አሁን ላይ ለረጅም ግዜ ሲደረግ የነበ ረው ትግል ወደ ወሳኝ የድል ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተገኘውን ድል ጠብቆና አድምቆ ለመሄድ የተደራጀና ህዝባዊ መሰረት ያለው ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው። ሆኖም አሁን ያለው አከባቢያዊና ሀገራዊ የፖለቲካ እውነታ ህዝባችን እና ያገኘውን ድል የሚመጥን ከመሆን በተቃራኒ ህዝባችን በጠየቀው ጥያቄ እንዲሸማቀቅና ጥፋተኝነት እንዲሰማው በማድረግ ከፍተኛ የሆነ የብቀላ ወጥመድ እየተዘረጋ ያለበትን ሁኔታ አስተውለናል። ህዝባችንን ዳግም በጨለማ ለመወርወር እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች ከግዜ ወደ ግዜ መልካቸውንና መጠናቸውን እየቀየሩ በህዝባችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የሞራል እና የስነ ልቦና ጫናዎችን እየፈጠሩ ቆይተዋል። ለአብነትም የሲዳማ ህዝብ ብዙ ዋጋ ከፍሎ ያገኘው በክልል የመደራጀት መብት የስልጣን ርክክብ እንዳይደረግና እንዲዘገይ ከዛም ባሻገር ከህዝባችን ፍላጎትና ውሳኔ ውጪ የሆነ ፖለቲካዊ መዋቅር ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ሙከራ የዚህ ሴራ ማሳያ ነው። ከዚህም ባለፈ ህዝባችን ድል ሊያስጠብቅ የሚችለውን ህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊና ህገ መንግስታዊ ስርዓትን አጠልሽቶ ለማሰናከል እየተደረገ ያለው ጥረት ይህ ነው የሚባል አይደለም። ለዚህ ሴራ ትግበራ ይሆን ዘንድ የሲዳማ ፖለቲካ ሊህቃኖችን፥አክቲቪስቶችን እና ጋዜጠኞች ላለፉት 7 ወራት ያለ ፍርድ በእስር እንዲሰቃዩ ተደርጎ የሚመሰረተውን የሲዳማ ክልል አቅም አልባና ደካማ አድርጎ ለማቅረብ የተኬደው ርቀት ከፍተኛ ነው። በህዝባችን ላይ እየተካሄደ
It's about Sidaama!