Skip to main content

ለፓርቲ ስልጣን የሚንሻኮትበት ወቅት ላይ አይደለንም!

ሲአን በሲዳማ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በአገሪቱ ባለው የፖለቲካ ተሳትፎ ረዥም እድሜ ካስቆጠሩ አንጋፋ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ይታወቃል። ድርጅቱ ላለፉት ከ 40+ አመታት የሲዳማን ህዝብ ፖለቲካዊ እና ዴሞክራሲያዊ ጥቅሞችን በማስቀደም ስሰራ ቆይቷል። ለዚህም በከፈለው ከፍተኛ መስዋእትነት ለሲዳማ ህዝብ ያጎናጸፋቸው በርካታ ድሎች በህዝቡ የታሪክ ማህደራት በኩራት ተመዝግበው ይገኛሉ።

ሌላው ቀርቶ ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ፣ የሲዳማ ህዝብ የራሱን ክልላዊ  መስተዳድር ዳግም ለማዋቀር በሚያደርገው ትግል ከየትኛውን ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት በበለጠ ፤ ከህዝቡ ጎን በመቆም እና የህዝቡን ድምጽ በማሰማት እኩሪ ተግባራትን አከናውኗል። 

ሲአን ለሲዳማ ህዝብ ከሰራው አኩር ተግባር የተነሳ ብቻ ሳይሆን፤ የሲዳማ ህዝብ በተለይ በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ ባለው የክልሉ ገዥ ፓርቲ የሚደርስበት የማግለል እና  ጸረ ሲዳማ አካሄድ ከመቼውም ጊዜ በላይ የሲአንን በሁለት እግር መቆም አንገብጋቢ አድርጎታል። የሲዳማ ህዝብ በማካሄድ ላይ ያለውን ፖለቲካዊ ትግል ከዳር ለማድረስ መሪ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን፤ መሪ ድርጅትም ያስፈልገዋል። አሁን ባለው ሁኔታ የሲዳማን ትግል በመምራት ከፍተኛ ሚና ሲጫውቱ የነበሩ ኤጄቶች በየእስር ቤቶች በመማቀቅ ላይ በመሆናቸው፤ እንደህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲነቱ የህዝቡን ትግል ለማስቀጠል፤ የሲዳማ ህዝብ የሲአንን መጠንከር ከምንም በላይ ይፈልገዋል።

ታዲያ በዚህ አንገብጋብ ወቅት ሲአንን አጠንክሮ ከመምራት ይልቅ፤ በተለይ አመራሮቹ ለፓርቲ ስልጣን ስሻኮቱ ይታያል። በሁለት ጎራ ተከፍለው በህጋዊነት ዙሪያ የሚጣሉት እነዚሁ አመራሮች፤ ያላቸውን ልዩነቶች ወደ ጎን ትተው የህዝቡን ፖለቲካዊ ጥቅም፤ ከማስቀደም ይልቅ ለራስ ህጋዊነት ስከራከሩ ተሰምቷል።

የሲዳማ ህዝብ በአፊኒ ባህሉ መሰረት መሰል ልዩነቶችን በስከኔ መልኩ፤ በሽማግሌ ፊት መፍታት እንደሚችል አመራሮቹ እያወቁ፤ ለራሳቸውም ሆነ ለሲዳማ ህዝብ ክብር በሌለው መልኩ፤ አደባባይ ወጥተው የህዝብ መሳቂያ እና መሳለቂያ እየሆኑ ይገኛል። ለሲዳማ ሽማግሌዎች ሳይሆን፤ ለአለም አቀፍ የህዝብ መገናኛ አውታሮች ያሉባቸውን ችግሮች ስዘረግፉ ታይተዋል። በጣም የሚያሳፍረው ደግሞ፤ ጸረ ሲዳማ በሆነው የደቡብ ሬድዮ እና ቴሌቭዥን ድርጅት ቀርበው ውስጠ ገበናቸውን መዘርገፋቸው፤ ለሲዳማ ህዝብ ጥሩ የማይመኙትን አካላት ሆድ ያረስ ሆኗል።

ይህ ወቅት የሲአን አመራሮች ብቻ ሳይሆኑ መላው ሲዳማ በተግባሩም ሆነ በቃሉ አንድ መሆን ያለበት ጊዜ ነው። ስለሆነም ጥለኛ አመራሮቹ የህዝቡን ፖለቲካዊ ጥቅም በማስቀደም ብሎም፤ የድርጅታቸውን የወደፊት ህልውና ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ ለአንድ አላማ ብታገሉ መልካም ነው።  



Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa