Skip to main content

‹‹ተማሪዎች ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምረው ነፃና ፍትሐዊ ምርጫን መለማመድ አለባቸው›› አቶ ስምዖን ከበደ፣ የማማከርና የሒሳብ ሥራ ባለሙያ

አቶ ስምዖን ከበደ የማማከርና የሒሳብ ሥራ ባለሙያ ሲሆኑ፣ ተማሪዎች ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምሮ ‹‹የምርጫ ሥርዓትንና ሒደት በየትምህርት ቤታቸው መለማመድ አለባቸው›› የሚል ሐሳብ ይዘው ተግባራዊ ለማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአገር ደረጃ ለሚታቀደው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አሁን ከሚታዩ የተለያዩ የፖለቲካ አተያዮችና ሥነ ሥርዓቶች ባሻገር፣ በጉዳዩ ላይ ከታችኛው ደረጃ ጀምሮ ልጆች ላይ ቢሠራ የተሻለ ውጤት ሊያመጣ ይችላል የሚል ዕምነት አላቸው፡፡ ይህንንም ዕቅድ ወደ ተግባር ለመቀየር የሚመለከታቸውን የመንግሥት አካላት ማነጋገር መጀመራቸውን ይገልጻሉ፡፡ በአጠቃላይ ምን ማድረግ እንዳቀዱና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ነአምን አሸናፊ አነጋግሯቸዋል፡፡
ሪፖርተር፡- ተማሪዎች የምርጫ ሥርዓትና አሠራርን ከትምህርት ቤት ጀምረው ሊለማመዱትና ሊያዳብሩት ይገባል የሚል ሐሳብ ይዘው በመነሳት፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድና ለትምህርት ሚኒስቴር አቅርበው እየሠሩ ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ያነሳሳዎት ምክንያት ምንድነው?
አቶ ስምዖን፡- የዚህ ሐሳብ መነሻ የስድስት ዓመት ልጄ ነች፡፡ ወደፊት ምን መሆን ትፈልጊያለሽ? ብዬ ስጠይቃት፣ ‹‹ዶ/ር ዓብይን መሆን እፈልጋለሁ፤›› የሚል ምላሽ ሰጠችኝ፡፡ ምላሿ አስደነገጠኝ፡፡ መደንገጤንም ዓይታ፣ ‹‹ሴት መሆን አትችልም እንዴ?›› ብላ ጠየቀችኝ፡፡ ይቻላል የሚል ምላሽ ሰጥቻት፣ እንደ ዶ/ር ዓብይ ለመሆን ግን ብዙ መሥራትና ራስን ማዘጋጀት እንዳለባት አስረዳኋት፡፡ በዚህ ጥያቄ መሠረት ሌሎች ተማሪዎችም እንዴት ራሳቸውን መቅረፅ ይችላሉ? ራሳቸውን እንዴት ማዘጋጀት ይችላሉ? ብዬ በማሰብ የዚህ ዓይነቱን አስተሳሰብ ለማዳበርና መሠረታዊ ነገር ሊያገኙ የሚችሉት በትምህርት ቤት በሚያደርጉትና በሚለማመዱት፣ የተማሪዎች ምርጫ ላይ ቢሳተፉ ነው ከሚል አስተሳሰብ የመነጨ ነው፡፡ ተማሪዎች በትምህርት ቤታቸው ውስጥ በሚያደርጉት ምርጫ በርካታ ነገሮች ሊማሩ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ በሚኖር የምረጡኝ ቅስቀሳና ሌሎች ከዚህ ሒደት ጋር የተያያዙ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ በርካታ ክህሎቶችን ሊያዳብሩና ዴሞክራሲያዊ ምርጫንም ሊለማመዱ ይችላሉ ከሚል እሳቤ የመነጨ ነው፡፡ ይህ ደግሞ እንደ አገር ለሚታሰበው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የራሱን ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል፡፡
ስለዚህ ልጄን እንዴት አድርጌ ነው ወደዚህ መስመር መክተት የምችለው? ጠያቂና ገለልተኛ ዜጋ አድርጌ መቅረፅ የምችለው? ብዬ ሳስብ ያገኘሁት ነገር ይህ ብቻ ነው፡፡ የሲቪክና የሥነ ምግባር ትምህርት እንደሚፈለገው ሊቀርፃቸው አልቻለም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡበት ትምህርት ቢኖር ሲቪክና የሥነ ምግባር ትምህርት ነው፡፡ በሀልዮት ደረጃ፣ በተግባር ግን ምንም ዓይነት ለውጥ እያመጡ አይደለም፡፡ ስለዚህ ራሳቸው ተማሪዎቹ እንዲለማመዱት፣ እንዲረዱትና በተግባር እንዲሞክሩት ለማድረግ ያለመ ሐሳብ ነው፡፡ ዴሞክራሲ አንዴ ተሠርቷል ተብሎ የሚቆም ነገር አይደለም፡፡ በየጊዜው መታደስና እንክብካቤ ይሻል፡፡ በተለያዩ ደረጃዎች ባህል መሆን አለበት፡፡ ይህን ለማድረግ ዋነኛ ማስተማመኛው ደግሞ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ነው፡፡ ስለዚህ የእኔ ሐሳብ ተማሪዎች ከታችኛው የትምህርት ደረጃ ጀምረው ነፃና ፍትሐዊ ምርጫን መለማመድ እንዳለባቸው ከማሰብ የመነጨ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- ስለምርጫ ስንነጋገርና በአገር አቀፍ ደረጃ ባህል እንዲሆን ሲሠራ በዋነኛነት የምርጫ ቦርድ ድጋፍና ተሳትፎ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አንፃር ከምርጫ ቦርድ ጋር ያለዎት ግንኙነት ምን ይመስላል? እነሱስ ሐሳብን እንዴት ተቀበሉት?

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa