Skip to main content

የሀዋሳ ሰላማዊ ሰልፍ በአገሪቱ ሚዲያዎች በጥቂቱ

ሀዋሳ የካቲት14/2011 የሲዳማ ህዝብ የክልል እንሁን ጥያቄውን ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ አቀረበ።
ከማለዳው ጀምሮ በተካሄደውና መነሻውን ከሃዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል አድርጎ መድረሻውን በአዲሱ የከተማ ስታዲዮም ባደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከሲዳማ ዞን 36 ወረዳዎች የተውጣጡ ቁጥራቸው በርካታ ህዝብ ተሳትፏል።
በሰልፉ ላይም ” የሲዳማ የክልል እንሁን ጥያቄ ህገመንግስታዊ ነው “፣ “ያለምልንም ደም ሪፍረንደም “፣ “ላቀረብነው የክልልነት ጥያቄ ሪፈረንደሙ በአስቸኳይ ይካሄድ ” እና ሌሎች መፈክሮችን ተሳታፊዎች ይዘው ወጥተዋል።
ከተሳታፊዎች መካከል የሲዳማ ወጣቶች ተወካይ ወጣት ታሪኩ ለማ “ባለፉት 27 ዓመታት አባቶቻችን የታገሉለት ራስን በራስ የማስተዳደር ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ ሀገራዊ ልዕልና አግኝቶ ህዝቡን እኩል ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ ባህልና ቋንቋችንን የማፈን ሥራ ሲሰራ ቆይቷል” ብሏል።
“ህገመንግስታዊ መብትን በመጠየቃቸውና የሲዳማን የክልል እንሁን ጥያቄ በማንገብ የወጡ በርካታ ወገኖቻችን ለእስራት፣ ለስደትና ለጉዳት ተዳርገዋል” ያለው ወጣት ታሪኩ የህዝቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊና ስነ ልቦናዊ መስተጋብር እንዲሁም ፖለቲካዊ ጥያቄው ግንዛቤ ውስጥ ሳይገባ መቆየቱን ተናግሯል።
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ስኳሬ ሹዳ በበኩላቸው እንዳሉት አንድ ዲሞክራሲያዊ ማህበረሰብ መገንባት የሚቻለው ሰጥቶ በመቀበል መርህ፣ በእኩልነትና እኩል በመጠቀም መብት ላይ በመመርኮዝ ነው።
የሲዳማ ህዝብ ላለፉት ዘመናት በተለያዩ ጊዜያት የክልልነትና ራስን በራስ የማስተዳደር መብቱን በህጋዊ መንገድ ለማስከበር ሲጠይቅ እንደነበርና ባለፉት ስርዓቶችም ጭምር ይህን መብቱን ለማስከበር ሲል እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የከፈሉ በርካታ ጀግኖች እንዳሉት አስታውሰዋል።
ውጤቱ ቢዘገይም እንኳን ትግል የሚደረገው አንድ ውጤት ለማምጣት በመሆኑ አሁንም ጥያቄ ተጠናክሮ መቀጠሉንና ሰላማዊ ሰልፉ የእዚህ ማሳያ መሆኑን  ተናግረዋል።
በሰላማዊ ሰልፍ ላይ የተነሱ የህዝብ ጥያቄና ቅሬታዎችን በየደረጃው ላለው የመንግስት አካል እንደሚያቀርቡ የገለጹት አቶ ስኳሬ፣ ጥያቄያቸው የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ አቅም በፈቀደ ሁሉ ከጎናቸው እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል።
የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቃሬ ጫዊቻ በበኩላቸው ” የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ወቅቱንና ህገመንግስቱን መሰረት አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የቀረበ የመብት ጥያቄ ነው” ብለዋል።
የዞኑ አስተዳደር ህዝቡ ያነሳውን ጥያቄ ለሚመለከተው አካል እንደሚያቀርብ ገልጸው ጥያቄው ፈጣን ምላሽ እንዲያገኝ የዞኑ አስተዳደር አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከተሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ከሸበዲኖ ወረዳ የመጡት አቶ ብርሀኑ ቢጣላ እንዳሉት ከእዚህ በፊት የህዝቡን ጥያቄ ሲያስተጋቡ የነበሩ ልጆቻቸው ለጉዳት ሲዳረጉ እንደነበር አስታውሰዋል።
በኤጀቶ ሰላም አስከባሪ የሆነው ወጣት ካሳሁን ተረጨ በበኩሉ እንዳለው ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ኤጀቶ ሰላም በማስከበርና በማስተባበር ስራውን በአግባቡ ሲሰራ ቆይቷል።
ዛሬ በሀዋሳ ከተማ የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ያለምንም ችግር በሰላም ተጀምሮ የተጠናቀቀ ሲሆን ቁጥራቸው ከአንድ ሺህ የሚበልጥ ኤጀቶዎች ሰልፉን በማስተባበር ለሰልፉ ሰላማዊነት የበኩላቸውን እገዛ ማድረጋቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

“ሕገ መንግሰታዊ መብታችን ይከበር” በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

ህገ መንግሰታዊ መብታችን ይከበር በሚል መሪ ቃል በሀዋሳ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ መሆኑን ተገለፀ።
በሰለማዊ ሰልፉ ከሲዳማ ዞን 36 ወረዳዎች እና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ነው።
የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች “ህገ መንግስታዊ መብታችን ይከበር! የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ መልስ ይሰጠው! የሪፈረንደም ቀን ይወሰን !” የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ይዘው ወጥተዋል።
መነሻውን ከሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ ዓለምአቀፍ ስታዲየም መዳረሻውን በማድረግ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
የደቡብ ክልል ምክር ቤት በጥቅምት ወር ባካሄደው በ10ኛ መደበኛ ጉባኤው የሲዳማ ብሔር በክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ተቀብሎ ለህዝበ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መምራቱ ይታወሳል። 
walta

በሰለማዊ ሰልፉ ከሲዳማ 36 ወረዳዎች እና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የተሳተፉበት ነው።
ሰለማዊ ሰልፈኞቹ “ህገ መንግስቱ ይከበር ! የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ መልስ ይሰጠው! የሪፈረንደም ቀን ይወሰን !” የሚሉና መሰል መፈክሮችን እያሰሙ ነው።
መነሻውን ከሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ያደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ ዓለምአቀፍ ስታዲዮም መዳረሻውን በማድረግ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ ከወራት በፊት ባደረገው በ10ኛ መደበኛ ጉባኤው የሲዳማ ብሔር በክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ተቀብሎ ለህዝበ ውሳኔ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መምራቱ ይታወሳል።
ebc
የሲዳማ ሕዝብ በብዛት የሚኖርበት አካባቢ የክልል መስተዳድርነት ሥልጣን ወይም መዋቅር እንዲሰጠዉ የሚጠይቅ ሰልፍ ዛሬ ሐዋሳ ዉስጥ ተደረገ። ኤጄቶ ተብሎ የሚጠራዉ የሲዳማ ወጣቶች ሰብስብ ባደረጀና በተቆጣጠረዉ ሠልፍ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ የሲዳማ ተወላጆች ተካፋዮች ነበሩ። የተለያዩ መፈክሮችን ያሰማና ያነገበዉ ሠልፈኛ ሐዋሳ ስታዲዮም ተሰብስቦ አሁን በዞን ደረጃ የተዋቀረዉ የሲዳማ መስተዳድር በክልል ደረጃ እንዲዋቀር ከዚሕ ቀደም ያቀረበዉ ጥያቄ ገቢራዊ ባለመሆኑ ቅሬታዉን ገልጧል።የሠልፉ ተካፋዮች በተለይም ወጣቶቹ ጥያቄያቸዉ ተገቢ፤ ሕዝባዊና ሕገ መንግሥታዊ በመሆኑ ባስቸኳይ ገቢር መሆን አለበት ይላሉ።የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪም ለሰልፈኛዉ ባደረጉት ንግግር ጥያቄዉ ተገቢ መልስ እንዲያገኝ መስተዳድራቸዉ የሚችለዉን ግፊት ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። ከሠልፉ በፊት ግጭትና ሁከት ይፈጠራል በሚል ሥጋት የሐዋሳ ከተማ አገልግሎት መስጪያ ተቋማት፣ ትምሕርት ቤቶችና መደብሮች በከፊል ተዘግተዉ ነበር። የሐዋሳዉ ወኪላችን ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ እንደዘገበዉ ግን በሠልፉ ምክንያት የተፈጠረ ግጭትና ሁከት የለም።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa