Skip to main content

የኤጄቶ አቋም መግለጫ

የሲዳማ ኤጄቶ አቋም መግለጫ
=====================
#ዛሬ በጥር 20 2011 ኣ/ም ታሪካዊው የሲዳማ ኤጄቶ ሁለተኛ ዙር ጋዶ በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መቀመጫ በሆነችው ሀዋሳ በወቅታዊ የህዝባዊን ጥያቄዎች እና ጥያቄው በደረሱበት ደረጃ ላይ ተመክሯል።
በመሆኑም ኤጄቶ ዛሬም ቢሆን ነገ የሰላም አማባሳደር ነው። የለውጡ መንግስታችንም በግልጽ እንደምያምነው ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው ለሰላም መደፍረስ ቁልፍ ምክንያት የሚሆኑ ችግሮችን ቀድሞ በመከላከልና ያልተመለሱ ዘመን ዘለቅ የሆኑ ህዝባዊ ጥያቄዎችን ህግን እና ደሞክራሲያዊ መርሆችን ተከትሎ መመለስ ሲቻል መሆኑ ይታመናል፡፡
#በመሆኑም ከዚህ በላይ የሲዳማን ክልል ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ ቀን ማራዘም ህዝብ ከመንግስት ጋር ያለውን መተማመን የሚሸረሽር ከመሆኑ ባሻገር የህዝብ ተቋማትን ገለልተኛነትና ህዝባዊ ውግንና ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ በመሆኑ መንግስት አከባቢያችንን ላልተፈለገ ውጥረት እና ስጋት ከሚያስገባ ጸር ህገመንግስታዊ አካሄድ በመቆጠብ አስቼኳይ ምላሽ ይሰጠን ዘንድ እንጠይቃለን።
በማጠቃለያም በዛሬው ጓባኤ ተወያይተን በሚከተሉት አቋሞች ላይ ተስማምተናል።
1 የሲዳማ ህዝብ ራሳችንን ችለን በክልል ልንደራጅ ጥያቄ በቀን 12/11/2010 ዓ.ም በተፃፈው ዳብዳቤ የዞኑ ምክር ቤት አጽድቆ ለደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ/ ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2011 ዓ.ም አቅርቦ ጥያቄያችን ህገ መንግስታዊ በመሆኑ በክልል ምክር ቤት ፀድቆ ሪፈረንደም እንድካሄድ አቅጣጫ አስቀምጦ ለኢፌዴሪ ምርጫ ቦርድ በቁጥር በቀን 12/3/2011 ዓ.ም በተፃፈው ደብዳቤ ህዝበ ዉሳኔ እንድናከናውን ጠይቀን የህዝበ ውሳኔውን ቀን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን ፡፡
ስለሆነም የሪፈረንደም ቀን በመዘገየቱ ህዝባችን ሌሎች ሰላማዊ የትግል አማራጮችን ለመጠቀም ስለሚገደድ ይህ ከመሆኑ በፍት በአፋጣኝ የረፈረንደም ቀን ይፋ እንድያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
2 ባሁን ግዜ የሲዳማ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር እንደ ዋና አጀንዳ ይዞ ከሚገኝበት የሪፈረንደም ቀነ ቀጠሮ ውጪ ያለ የትኛውም አጀንዳ በምንም መስፈርት ተቀባይነት የለውም። በዚህም የጄቶን የትግል ወኔና ትኩረት የሚፈታተኑ አጀንዳዎችን ይዘው የሚቀርቡ ሀይሎች አደብ እንዲገዙ እንጠይቃለን።
3 በዚህ ሳምንታት የክልል ብሎም የሁለቱም መዋቅር አመራሮች የክልል ጥያቄያችን በደረሰበት ደረጃ ላይ አስቼኳይ መግለጫ ወይም ምላሽ እንዲሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
4 ለክልል ማቋቋሚያነት የተሰየምው ታስክ ፎርስ ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶችም እስካሁን የደረሰበትን ደረጃ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡
#በመጨረሻም የተከበራችሁ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የደቡብ ክልል ህዝቦች ብሎም መላው የኢትዮጵያ ህዝቦች የሲዳማን ህዝብ አቃፊነት እና እንግዳ አክባሪነት ከናንተ በላይ የሚመሰክር አለመኖሩ ለሁሉም ግልጽ ነው።
የናንተና የኛ ትስስር በደቡብ ክልል ህልውና ላይ የተመሰረት ባለመሆኑ ክልሉ ብፈርስ አንድነታችን የሚሸረሸርበት ምንም ምክንያት አይኖርም። #ከዚህ መነሻም ከሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ጋር በመሰለፍ ኤጄቶ ከጸረ ህዝብ እና ጸረ ህገመንግስት ሀይሎች ጋር እያደረገ ያለውን ትግል እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን።
#ኤጄቶ
#ሀዋሳ_ሲዳማ_ኢትዮጵያ🇪🇹

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa