Skip to main content

በአገሪቱ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግርና ስጋት እንዲወገድ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ልዩነት እንዲሰሩ ተጠየቀ

ሐዋሳ ታህሳስ 3/2011 በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋለ ያለው የጸጥታ ችግርና ስጋት እንዲወገድ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ልዩነት እንዲሰሩ የሰላም አምሳደሮች ጠየቁ።
ከዘጠኝ ክልሎችና ሁለት ከተሞች አስተዳደሮች የተውጣጡ ሴት የሰላም አምባሳደሮች ቡድን በደቡብ ክልል ሀላባና ሐዋሳ ከተሞች በመገኘት ከኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል፡፡
የቡድኑ መሪ በሰላም ሚኒስቴር የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ተገኝ በሀላባ ከተማ ከደቡብ ክልል ሴቶች ማህበር አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ላይ እንዳመለከቱት ኢትዮጵያውያን በዘር፣ በሃይማኖትና በብሄር ሳይከፋፈሉ  ከችግሮቻቸው ለመውጣት በጋራ መነሳት ይጠበቅባቸዋል።
ሰላም ለአገር ልማትና ዕድገት ወሳኝና ቁልፍ መሣሪያ  መሆኑን አመልክተው ሁከትና ግርግር በሚከሰትባቸው አካባቢዎች ከማንም በላይ ተጎጂ የሚሆኑትን ሴቶች ከጉዳት ለመጠበቅ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
ወንዶች ከማንም በላይ የእናታቸውንና የባለቤቶቻቸውን ሐሳብ እንዲተገብሩ የጠየቁት ወይዘሮ አበባ፣ ሚኒስቴሩ ከሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ያቋቋመው ቡድን በክልሎች እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በቡድኑ የሐረሪ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ገነት አሰፋ እንዳሉት ሴቶች በጸጥታ እጦት ምክንያትም ጉዳት ሰለባ ከመናቸውም በላይ፤ለልጆቻቸውና ለባሎቻቸው ደህንነት በማሰብም በስጋት እንደሚኖሩ ተናግረዋል።
’’እኛ እናቶች ልጅ ወልዶ እስከማሳደግ ባለው ሂደት ለራሳችን ልብሳችንን እየሰፋን ለልጆቻችን አዲስ ገዝተን እያለበስን ከሰው በታች እንዳይሆኑብን ስናስተምር ኖረን መጨረሻ ላይ ግን ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱ ሬሳቸው የሚመጣበት ሁኔታ ነው ያለው’’ ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ሴቶች ማህበር ሊቀመንበር ወይዘሮ አስቴር ይርዳ እንዳሉት በሰላም እጦት ከማንም በላይ ተጎጂ የሚሆኑትን ሴቶች ለመታደግና  ቤተሰባቸውን ለመጠበቅ የሰላምን ጠቀሜታ ማስተማር እንደሚገባቸው አመልክተዋል፡፡
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን እንዳሉት ዞኑ ከሌሎች አካባቢዎች በአንጻራዊ ሁኔታ ሰላም የሚታይበት ቢሆንም፤ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የሐሳብ ልዩነቶችን በማቻቻል የአካባቢያቸውን ብሎም የአገሪቱን ሰላም ለማስጠበቅ ከሕዝቡ ጋር ተቀናጅተው እንደሚሰሩ አስታውቀዋል፡፡
በተመሳሳይ በሀዋሳ ከተማ በተደረገው ውይይት የከተማዋ የአገር ሽማግሌ አቶ ጥላሁን ቱቴ እንዳሉት የአገሪቱን ሰላም ለማደፍረስ የሚደረገው እንቅስቃሴ ሕዝብን መናቅ በመሆኑ ሊቆም ይገባዋል ብለዋል፡፡
ጥቂት ግለሰቦች በተለያዩ አካባቢዎች በሚያስነሱት ችግር እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለማስቀረት የጋራ ጥረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም  አመልክተዋል፡፡
ሌላው የአገር ሽማግሌ አቶ ቡኒሳ ቡልቡላ በበኩላቸው የነገዪቱ ኢትዮጵያ የዘር፣ የሃይማኖትና የጎሣ ልዩነት እንዳይኖርባት እንሰራለን ብለዋል፡፡
ቡድኑ ያስረከበውንን አደራ ተቀብለው ከቤተሰብ ጀምሮ በሰላም ጉዳይ ላይ የጋራ አቋም ለመያዝ እንደሚጥሩም ተናግረዋል፡፡
ቡድኑ 21 ሴቶች በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፣እስካሁን በስምንት ክልሎች በመዘዋወር በሰላም ዙሪያ ከኅብረተሰቡ ጋር ተወያይቷል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa