Skip to main content

Posts

Showing posts from November, 2018

ኢ/ር ታከለ ኡማ ከሀዋሳ ከተማ ወጣቶችን ጋር ተወያዩ

 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከሀዋሳ ከተማ ወጣቶች ጋር ተወያዩ። ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በውይይታቸው ለሀዋሳ ከተማ ወጣቶች እንደተናገሩት ኢትዮጵያዊነት ከፍታ ነው ብለዋል። የከፍታችን ዋና ምሰሶው ፍቅር ሲሆን፥ ሀዋሳ ከተማ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች በመተሳሰብ እና በመፈቃቀድ ከፍታቸውን ጠብቀው በጋራ የሚኖሩባትና በምሳሌነትም የምትጠቀስ ከተማ ነች ብለዋል። የሀዋሳ ከተማ ወጣቶች ይህን አረዓያነት የማስቀጠል ኃላፊነት እንደለባቸውም አሳስበዋል። ወጣቱ ትውልድ ተራራ ለመውጣት ብሎም አስፈለጊ ሆኖ ሲገኝ መናድ የሚችለው ኢትዮጵያዊ ከፍታውን ሲጠብቅ ብቻ ነውም ብለዋል። አልፎ አልፎ ከዚህ ከፍታችን የሚያወርዱ ትርክቶች ተከትሎ የሚፈጠሩ ችግሮች ለችግር የሚዳርጉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። እነዚህን ችግሮች ለማስወገድ ደግሞ አብሮነት፣ ፍቅር መተሳሰብ፣ መፈቃቀድ መሆኑን ነው ያመላከቱት። አባቶቻችን የኢትዮጵያ ዳር ድንበር በማስከበር የተዋደቁት የኢትዮጵያን ከፍታ ለዚህ ትውልድ ለማስተላለፍ ነው ብለዋል። ምንጭ 

ምክር ቤቱ የዕርቀ ሰላም ኮሚሽንና የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያየ

(ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት አካሂዷል። ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው የዕርቀ ሰላም ኮሚሽንና የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ አዋጅን ጨምሮ የፌደራል መንግስት አስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ማሻሻያ ተመልክቷል። ምክር ቤቱ የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን፥ ለውጭ ሰላምና ደህንናት እና በተበባሪነት ለህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር እይታ መርቷል፡፡ እንዲሁም የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ምክር ቤቱ በዛሬው ስብሰባው ውይይት አድርጓል። በረቂቅ አዋጁ ላይ የተወያየው ምክር ቤቱ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ለውጭ ግንኙንና ሰላም ጉዳዮች እና በተባባሪነት ለህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች ለዝርዝር እይታ መርቷል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት የብሄራዊ እርቀ ሰላም ኮሚሽን እና የማንነትና የወሰን ኮሚሽን እንዲቋቋሙ በመወሰን እንዲፀድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መላኩን ተከትሎ ነው ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጆቹ ላይ የተወያየው። የብሄራዊ እርቀ ሰላም ኮሚሽን በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ግጭቶች ምከንያት በህዝቦች መካከል የተደራረቡ የቁርሾ ስሜቶችን ለማከም፤ እውነት እና ፍትህ ላይ መሰረት ያደረገ እርቅን ለማውረድ የሚያግዝ መሆኑም ተገልጿል። የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጉዳዮች ኮሚሽን ደግሞ በክልሎች የአስተዳደር ወሰንና በማንነት ጥያቄዎች ዙሪያ በተደጋጋሚ የሚነሱ ችግሮችን ሀገር

As Southern Nations break free, pressure mounts on EPRDF

Analysis As Southern Nations break free, pressure mounts on EPRDF November 28, 2018 by   William Davison ,  Kulle Kursha Sidama progress towards statehood triggers copycat moves SNNP break-up is potential problem for SEPDM and EPRDF Splits and reforms leave federal system’s future in question  F or almost a quarter of a century, despite all of the Ethiopian federation’s problems, its architecture has remained intact, including the nine regional states etched into the constitution. That now looks set to change, dramatically. Following the Southern Nations, Nationalities and Peoples’ (SNNP) State Council’s  decision  last month to approve a request for a referendum on Sidama statehood, copycat moves are gathering pace across the multi-ethnic region. On Nov. 26, Gurage Zone Council voted to proceed with the process. Two weeks prior, Wolayta Zone affirmed a statehood  request , which will now be sent to the SNNP council for approval. Kaffa Zone also  approved

Women’s knowledge and associated factors on preconception care at Public Health Institution in Hawassa City, South Ethiopia

Objective Preconception care is pivotal to improve pregnancy and birth outcome. It is vital for the future health of mother, her child and her family, which is routinely practice. The study aims to assess knowledge of preconception care and associated factors in post natal women at public health institution in Hawassa city, South Ethiopia. Results In this study 20% (95% CI 16.9, 23.1) of post natal women at public health institution had a good level of knowledge on preconception care. Women who have secondary and above education level, urban residence, and have at least one ANC contact had significantly higher odds of good level of knowledge on preconception care. The finding of this study showed that level of women’s knowledge towards preconception care to be low compared to other studies. Having at least one ANC contact, urban residence and having secondary and above education are predictors of knowledge on preconception care. It shall be beneficial if the city health admi

የአዲስ አበባ ወጣቶች ወደ ሃዋሳ አቀኑ

(ኤፍቢሲ) የአዲስ አበባ ወጣቶች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠነከር ወደ ሃዋሳ አቀኑ፡፡ በዛሬው ዕለት ወደ ሐዋሳ ያቀኑት 300 የሚሆኑ የመዲናዋ ወጣቶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የልዑካን ቡድኑ በሁለት ቀናት የሃዋሳ ቆይታው የህዝብ ለህዝብ ውይይትን ጨምሮ በመዲናዋ ወጣቶች ዘንድ የተጀመረው የበጎ ፈቃድ ባህል በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲስፋፋ ለማስቻል ይወያያል ተብሏል፡፡ እንዲሁም ጉዞው በአዲስ አበባ እና በየሀዋሳ ከተሞች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር የሚደረግ መሆኑ ተነግሯል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶች በቀጣይነትም የሚያካሂድ መሆኑን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ምንጭ 

Livestock production under changing environment: CLIFOOD SDG Graduate schools running an international workshop at Hawassa University

Yesterday, the Block Seminar “Intensification of African Livestock Systems in a Changing World” started at the College of Agriculture, Hawassa University. The Block Seminar is part or the qualification program within German-Ethiopian SDG Graduate School: Climate Change Effects on Food Security (CLIFOOD), established between the Food Security Center, University of Hohenheim (Germany) and the Hawassa University (Ethiopia). The main objective of the CLIFOOD is the Education of African students at the (post)doctorate level to address threats of Climate Change to food Security in the Eastern African region. During the next 5 days the participants will learn about different aspects of livestock production: Nutrition and feed science, Animal breeding and husbandry, Livestock systems development, Environmental impacts of livestock farming, Future contribution of livestock to sustainable food and nutrition security. Also the CLIFOOD scholars will present and discuss results of their researc

ደኢሕዴን ከጠቅላላ ጉባዔ አቅጣጫ በማፈንገጥ ዞኖች ክልልነትን እያፀደቁ ነው አለ

የደኢሕዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) በደቡብ ክልል የሚስተዋለው የዞኖች የክልልነት ጥያቄን በዞን ምክር ቤቶች የማፅደቅ ተግባር ሕገ መንግሥታዊ ቢሆንም፣ ድርጅቱ በአሥረኛ ጉባዔው ካስቀመጠው አቅጣጫ ውጪ ነው አለ፡፡ ድርጅቱ ይኼንን ያለው ሰኞ ኅዳር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ያካሄደው አስቸኳይ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ ሲጠናቀቅ ነው፡፡ የድርጅቱ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ከስብሰባው በኋላ በሰጡት መግለጫ፣ ውሳኔዎች ለአፈጻጸም አስቸጋሪ በሆነ መንገድ እየተላለፉ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ የደኢሕዴን ጉባዔ ከኢሕአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ አንድ ቀን ቀደም ብሎ መስከረም 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ሲጠናቀቅ፣ በክልሉ ለረዥም ጊዜ ሲንከባለሉ የመጡ የሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጣቸውና የልማት ተጠቃሚነት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችም በአዲስ አደረጃጀቶች እንዲፈቱ አቅጣጫ ማስያዝን አስታውቆ ነበር፡፡ ለዚህም አፈጻጸም የተለያዩ ኮሚቴዎች ሲዋቀሩ፣ የክልሉ መንግሥትም የልማትና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን መመለስ የሚያስችሉ መፍትሔዎችን ለመስጠት ጥናት እያደረገ መሆኑን፣ ካሁን በፊት ከሪፖርተር ጋር ቆይታ ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ይሁንና በሐምሌ 2010 ዓ.ም. በዞኑ ምክር ቤት ፀድቆና በክልል ምክር ቤት ከወር በፊት ተቀባይነትን በማግኘት ሕዝበ ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ የሚገኘው የሲዳማ የክልልነት ጥያቄን ተከትሎ፣ በርካታ የክልሉ ዞኖች በዞን ምክር ቤቶች ደረጃ የክልልነት ጥያቄን እያፀደቁ ይገኛሉ፡፡ እስካሁንም ወላይታ፣ ካፋና ጉራጌ ዞኖች የክልልነት ጥያቄዎችን ያፀደቁ ሲሆን፣ በሌሎች ዞኖችም በተለያዩ ጊዜያት በሚስተዋሉ ሠል

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሎ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር

ማክሰኞ ኅዳር 18 ቀን 2011 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በአገሪቱ ስለተጀመረው ለውጥ፣ እንዲሁም በመጪው ዓመት ስለሚደረገው ምርጫ አስመልክቶ ተወያዩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተወያዩት ጥሪ ከተደረገላቸው የ80 ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ነው፡፡ ለውይይት የመነሻ ሐሳብ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገሪቱ አሁን ካለችበት የለውጥ ሒደት፣ በመጪው ምርጫ እንዲሁም ድኅረ ምርጫ ወቅት በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ከመገንባት አንፃር ሊከናወኑ ይገባል ያሏቸውን ዓበይት ነጥቦች በሦስት ምዕራፎች በመክፈል ይፋ አድርገዋል፡፡ የመጀመርያው ምዕራፍ የውይይቱ መክፈቻ መሆኑን በመጥቀስ፣ በዚህ ምዕራፍም በቀጣይ የሚካሄዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ምን ዓይነት መልክ ይኑረው በሚለው ሐሳብ ላይ ተወያይቶ ቀጣይ ውይይቶችን የሚመራ መመርያ ማዘጋጀትን እንደሚያካትት ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በውይይቱ ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ፣ በአጭር በመካከለኛና በረዥም ጊዜ መፍትሔ ሊበጅላቸው የሚገቡ ችግሮችን መለየት፣ ከዚህ ቀደም ሲደረጉ በነበሩ ውይይቶች ያጋጠሙ ችግሮችን መለየትና መፍትሔ ማስቀመጥ የሚሉት ነጥቦችም ተካተዋል፡፡ ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ ዋነኛ ትኩረቱን በመጪው ዓመት በሚካሄደው ምርጫ ላይ ትኩረቱን በማድረግ ምርጫው ነፃ፣ ተዓማኒና ፍትሐዊ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ሥራዎችን በተመለከተ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነ ነው የገለጹት፡፡ በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ደግሞ በዋነኛነት በምርጫ ሕጉ፣ በምርጫ ቦርድ ስያሜና አቅም ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፣ ከእነዚህ ከሕግና ከአሠራር ጉዳዮች በተጨማሪም በቅርቡ ወደ አገር ቤት የተመለሱ የፖለቲካ ቡድኖችን ምዝገባ በተመለከተ በጋራ መሥራት የ

Ethiopian Sidama Television Proram - የሲዳማ ቴሌቪዥን ፕሮግራም የሲዳማን የወላይታ እርቅን 1...

QPM planting (in Sidama)

Ethiopian Sidama Zone Bensa Woreda Coffee - ሲዳማ ዞን በንሳ ወረዳ የቡና ምርታማነትና የ...

በዞን ም/ቤቶች የሚነሱ የክልልነት ጥያቄዎች ከጉባኤው አቅጣጫ ውጭ ናቸው - ደኢህዴን

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ባሉ አንዳንድ የዞን ም/ቤቶች የሚነሱ የክልልነት ጥ ያቄዎች ከደኢህዴን ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ ጽ/ቤቱ ይህን ያስታወቀው የደኢህዴን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጉን ተከትሎ ነው። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ እንዳሉት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን አፈፃፀም ሂደት ገምግሟል፡፡ አስተዳደራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ ዝርዝር ጥናት እየተደረገ መሆኑን የጠቀሰው ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥናቱ ሲጠናቀቅ በጉባኤው የፀደቁ አዳዲስ የመዋቅር አደረጃጀቶች በክልሉ ም/ቤት ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው እንደሚቋቋሙ ገልጿል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ እየተበራከቱ የመጡትን የክልላዊ አደረጃጀት ጥያቄዎች በተመለከተም ጥልቅ ጥናት የሚያደርግ ከባለሙያዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ ቡድን መቋቋሙ ተገልጿል፡፡ ጥናቱን ተከትሎም ተገቢው ምላሽ እንደሚሰጥና ከዚህ ውጭ በዞን ም/ቤቶችና በተለያየ መልኩ የሚነሱ ጥያቄዎች ከድርጅቱ ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን አቶ ሞገስ በመግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡ ተቋማትን በመዝጋትና የዜጎችን ነፃ እንቅስቃሴ በመገደብ ሃሳብን በኃይል ለመጫን የሚደረጉ ተግባራት ተቀባይነት የላቸውም ያለው ኮሚቴው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የኅብረተሰቡን ጥያቄዎች ተከትሎ በተከሰቱ ግጭቶች በደረሰው የህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንም መግለፁን የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ተናግረዋል፡፡

Prevalence of adverse birth outcome and associated factors among women who delivered in Hawassa town governmental health institutions, south Ethiopia, in 2017

Prevalence of adverse birth outcome and associated factors among women who delivered in Hawassa town governmental health institutions, south Ethiopia, in 2017 Plain English summary Most pregnancy and childbirth is a joyful experience. But it sometimes end up in adverse birth outcome which disrupt the family condition leading to high individual and social costs. Adverse birth outcome in current study includes pregnancy loss/miscarriage, congenital anomaly or birth defect, preterm baby, low birth weight, perinatal death, macrosomia and intrauterine growth restriction. Most risk factors contributing to adverse birth outcome are amenable to modification. These poor reproductive life planning, substance use, abnormal pre-gestational BMI, irrational medication use, exposure to environmental toxin and contaminants, underlying chronic pre-gestational diseases, anemia and folic acid deficiency, poor regular exercise and physical activity, and presence of stress are included. The cur

ETHIO CALI - "Sidama De Cali" (Live at Music Tastes Good 2018 in Long Be...

በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና ከባህር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ

(ኤፍ.ቢ.ሲ) ዛሬ ከሰዓት በተካሄደ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 3ኛ ሳምንት ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከባህር ዳር ከተማ አቻ ተለያይተዋል። ሃዋሳ ላይ በተደረገው ጨዋታ አዲስ ግደይ በ14ኛው ደቂቃ በፍፁም ቅጣት ምት ጎል አስቆጥሮ በሲዳማ ቡና መሪነት እየተካሄደ ባለበት ወቅት፥ ጨዋታው ለደቂቃዎች ተቋርጦ ቆይቷል። የተቋረጠው ጨዋታ እንደገና ቀጥሎ በሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ የባህርዳር ከተማው ዳንኤል ሃይሉ ቡድኑን አቻ ያደረገችውን ጎል በ48 ደቂቃ አስቆጥሮ ጨዋታው በአቻ ውጤት ተጠናቋል። 3ኛው ሳምንት መርሃ ግብር ነገ እና ከነገ በስቲያም ቀጥሎ የሚካሄድ ይሆናል። በዚህም ነገ ደቡብ ፖሊስ ከደደቢት ሲጫወቱ በማግሰቱ እሁድ ደግሞ፥ ሃዋሳ ከተማ ከወላይታ ዲቻ እንዲሁም ስሑል ሽረ ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ።

በሲዳማ ዞን የሚገኙ እጅግ አስደማሚ የተፈጥሮ ቦታዎች

ከኤጄቶ የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በቀን ህዳር11/2011 ዓ/ም ከኤጄቶ የተሰጠ የአቋም መግለጫ ==================================== የሲዳማ ህዝብ በ130 ዓመታት የትግል ታሪክ ራሱን በራሱ በማስተዳደር በኢትዮጵያ ካሉ መንግስታት አንዱ ሆኖ ለሐገር ዕድገትና አንድነት የበኩሉን ለመወጣት የሞት፤የእስራት፤የስደትና ሌሎች ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶችም በበርካታ ዜጎቹ እየተፈጸሙበት መቆየታቸዉ ሃቅ ነዉ፡፡ ህዝባችን ይህንን ፍዳ እንዲቀምስም ምክንያት የሆኑ ከራሱ አብራክ የወጡ ባንዳዎችና ሌሎች የሲዳማን እሴት የማያዉቁ መሆናቸዉን በመገንዝብ በጽኑእ እየታገለ መምጣቱን ሰማዕታቱ ምስክሮች ናቸዉ፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በልዩ ሁኔታ የህዝቡ ጥያቄ መሥመር እንዲገባ ህዝቡ በምክር ቤቱ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ በህ-ገመንግስቱ መሠረት ሪፈረንደም መካሄድ እዳለበት ቢታወቅም ሳይደራጅ ወራቶች በመቆጠራቸዉ ይህንን ተግባር የሚመለከታቸዉ ሁሉ በፍጥነት ማድረግ እንዲችሉ ኤጄቶ አቋሙን በሰላማዊ መንገድ ለመግለጽ ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫ ዛሬ በቀን ኅዳር 11/2011 ዓ.ም ያስተላልፋል፡፡ 1. በሲዳማ ዞንና በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ያለዉ ከከፍተኛ አመራር እስከ ቀበሌ ድረስ ያለዉ ሪፎርም በአስቸኳይ የሐገራዊዉን እይታ መሠረት በማድረግ እንዲካሄድ በሙሉ ድምጽ ተስማምተናል፡፡ይህ ለዉጥም የህዝብ ዉግንና ያላቸዉ፤የህዝብ ችግር የወላዳቸዉ፤ከሌብነትና ከጠባብነት ራሳቸዉን ያጸዱ፤የተሸለ የትምህርትና ብቃትና ክህሎት ያላቸዉ፤በስነ-ምግባርና በሥራ ምስጉንነታቸዉ ብቻ የታነጹ እንዲሁም ወጣቱትን ኃይል መሠረት ያደረገ ሪፎርም እንዲደረግ በትጋት እንሠራለን፡፡ 2. የሪፈረንደም ጉዳይ በእጅጉ ፈጥኖ የማይካሄድበት ሁኔታ ተፈጥሮ ሲገኝ ቀጥለን ለምንወስደዉ እርምጃ መንግስት

Commentary: Sidama-Wolayta conflict: a pristine myth turning into reality? Hoola Halaleho

Commentary: Sidama-Wolayta conflict: a pristine myth turning into reality? Hoola Halaleho : “To this end, it is worth mentioning a peace and reconciliation conference which was held in Hawassa city yesterday between the two communities as a step in the right direction.”  Ambaye Ogato (PhD), For Addis Standard  Addis Abeba, November 19/2019 – It has now become evident that the country has ...

ዜጎች የሰላምና አንድነትን ጥቅም በመረዳት በጋራ እንዲቆሙ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አሳሰቡ

ሐዋሳ ህዳር 9/2011 ዜጎች የሰላምና አንድነትን ጥቅም በመረዳት በጋራ እንዲቆሙ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ አሳሰቡ። የሲዳማና የወላይታ ሕዝቦች የይቅርታና የእርቅ ሂደት ዛሬ በሐዋሳ ከተማ ተከናውኗል። ርዕሰ መስተዳድሩ በእርቀ ሰላም ጉባዔው ማጠቃለያ ላይ እንዳስገነዘቡት ዜጎች ሰላም ለሰው ልጆች ያለውን ተኪ የለሽ ሚና በመረዳት  ሰላማቸውን ለማስከበርና ለአንድነታቸው በጋራ ሆነው መንቀሳቀስ  ይጠበቅባቸዋል፡፡ የሲዳማና የወላይታ ሕዝቦች ያደረ ቁርሾ የሌላቸው ዘመናትን በአብሮነትና አስቸጋሪ ጊዜያትን በጋራ ያሳለፉ ጠንካራ ማህበራዊ ትስስር ያላቸው ሕዝቦች በመሆናቸው ለሰላም ተገቢው ዋጋ ሰጥተው መኖር እንደሚገባቸውም ገልጸዋል፡፡ በአገሪቱ የታየውን ለውጥ የማይፈልጉ አካላት የብሄርና የሃይማኖት መልክ ያላቸውን ግጭቶች ለመፍጠር ያሴሩ ነበር ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ አምና የተፈጠረው ችግር ሕዝቦቹን እንደማይወክል ተናግረዋል፡፡ መገናኛ ብዙኃን የሕዝቦችን አንድነት፣ ሰላምንና ፍቅርን በማሳደግ መጠቀም እንደሚገባ አቶ ሚሊዮን አሳስበዋል። ግጭቱ በሽምግልና በመፈታቱ የተሰማቸውን ደስታ የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በሰለጠነ መንገድ ሰላም በመውረዱ ሁለቱም ሕዝቦች አሸናፊዎች ናቸው ብለዋል፡፡ የሁለቱን ወንድማማች ሕዝቦችን አንድነትና ትስስር ለመመለስ ለጣሩ አካላት ምስጋና፣ የይቅርታና የእርቅ ሂደቱ እንዲሳካ ላደረጉ የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሸማግሌዎችና ለአስታራቂ ኮሚቴ አባላት ደግሞ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በሕዝቦች መካከል ግጭት የሚፈጥሩ አካላትን በጥንቃቄ መከታተልና የቀደመ ማህበራዊ እሴቶችን ማጎልበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ሰላም በእጃችን ያ

Ethiopian Sidama & Wolayta - የሲዳማና የወላይታ እርቅና የኮንታ ዞን ይገባናል ጥያቄ ይመልከቱ

Ethiopian Sidama Television Program - የሲዳማ ቴሌቪዥን ፕሮግራም 04/03/11ዓ.ም

በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ የዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ ተካሄደ

(ኤፍ.ቢ.ሲ) በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ የዕርቅና የሰላም ኮንፈረንስ በሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል አዳራሽ ዛሬ ተካሄደ። በዕርቁ ሥነ ሥርዓት ላይ ከሲዳማና ወላይታ ዞን የተወጣጡ የኃይማኖት መሪዎችና አባቶች፣ ከሁለቱም ዞኖች የተወጣጡ የባህል ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የኦሮሞ አባ ገዳዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ነዉ የዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ ዛሬ የተካሄደዉ። በኮንፈረንሱ የተገኙት የደኢህዴን ሊቀ መንበርና የኢፌደሪ የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሀት ካሚል፥ በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል በተፈጠረዉ የዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ ላይ በመገኘታቸዉ የተሰማቸዉን ደስታ ገልፀዋል። ይህን ዕርቅ ኢንዲመጣ የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ ላደረጉት ሁሉ አክብሮታቸዉንና አድናቆታቸዉን አቅርበዋል።

የሲአን ዓለም አቀፍ ድጋፍ ምክር ቤት የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ እንደሚደግፍ አስታወቀ

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) ሲዳማ ዞን ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር ላለፉት 40 ዓመታት የታገልኩለት ዓላማ በመሆኑ የምደግፈው ዕርምጃ ነው ሲል አስታወቀ፡፡ የሲአን አመራሮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡና እንዲታገሉ ጥሪ ካቀረቡ በኋላ ወደ አገር ውስጥ መግባቱን በማስታወቅ፣ ሲዳማ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖረው አስተዋፅኦ የጎላ እንዲሆን ለማድረግም እሠራለሁ ሲል አስታውቋል፡፡ ‹‹የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ በተለየ መንገድ የሚረዱ ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ይሁንና የብሔር ማንነትና ኢትዮጵያዊነት አብረው የሚሄዱ ናቸው ብለን ስለምናምን፣ ለዚህ ጥያቄ መልስ በመሰጠቱ ከማንም በላይ ዘብ የምንቆምላት ኢትዮጵያ ነች የምትኖረው፤›› ሲሉ፣ የንቅናቄው ዓለም አቀፍ ድጋፍ ምክር ቤት ሰብሳቢ በዛብህ በራሳ (ዶ/ር) ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡ ስለዚህ ይህ ውሳኔ ወደ ተግባር እንዲገባ በፍጥነት ሕዝበ ውሳኔ ተደራጅቶ ሲዳማ ራሱን በራሱ ማስተዳደሩ ዕውን እንዲሆን ጥሪ በማቅረብ፣ ‹‹ሲዳማ የኢትዮጵያ አካል ሆኖ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ያለባት ኢትዮጵያ እንድትኖር፣ የበኩላችንን አስተዋፅኦ ለማድረግ ዝግጁ ነን፤›› ብለዋል፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ደጀኔ ወልደ አማኑኤል የብሔር ግጭቶችን በተለይም የወላይታና የሲዳማ ብሔር ግጭቶችን በማነሳሳት የሲዳማን ጥያቄ ሌላ መልክ ለማስያዝ ጥረት የሚያደርጉ አካላት አሉ ካሉ በኋላ፣ ‹‹በመሠረቱ የሲዳማና የወላይታ ፍላጎት ምንም የሚያጋጭ አይደለም፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡ ‹‹ሁለቱም የራሳቸው አስተዳደር ተሰጥቷቸው በሰላም እንድንኖር ነው የምንፈልገው፤›› ብለዋል፡፡ በቀጣይ ምርጫ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን ፓርቲያቸው ብቁ ዝግጅት ማድረጉን፣