Skip to main content

የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቃሬ ጫዊቻ በዞኑ ውስጥ በቀጣይ በትኩረት የሚሠሩ ሥራዎች እና ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

Image may contain: 1 person, sitting, table and indoor
የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በቅርቡ የተሾሙት አቶ ቃሬ ጫዊቻ በዞኑ በየአከባቢው የረጅም ጊዜ የህዝብ ጥያቄና የመልካም አስተዳደር ችግር ሆነው የቆዩ ጉዳዮችን የህዝብን ፍላጐት መሠረት ባደረገ መልኩ ለመፍታት እንደሚሠሩ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡

በሀገራችን የተፈጠረው የለውጥ ሂደት የሲዳማ ህዝብም የሚጋራው በመሆኑ ይህንን ለውጥ ማስቀጠልና የህዝባችንን ፍላጐት ማርካት የመጀመሪያውና ዋናው ተልዕኳቸው መሆኑን ጠቁመው የሲዳማ ህዝብ ለሠላም፣ለልማት፣ለእድገት ቅድሚያ የሚሰጥና ከሌሎች ብሔሮችና ብሔረሰቦች ጋር ተፋቅሮና ተከባብሮ የመኖር ባህሉን በተግባር ያሳዬ፤እንግዳ ተቀብሎ ዘመድ የማድረግ ተምሳሌትነቱ ለሌላውም የሚተርፍ እሴት ያለው ህዝብ መሆኑን አመልክተው ህዝቡ ልዩነት የሚያጐሉ፣የሀገሪቱን እድገት የሚያጓትቱ የተሳሳቱ አመለካከቶችን ወደ ጐን በመተው ከአጐራባች ክልሎችና ዞኖች ጋር እንዲሁም በውስጡ ከሚኖሩ ሌሎች ብሔረሰቦች ጋር በፍቅርና በሰላም አብሮ የመኖር እሴት ለረጅም ዘመናት ያጐለበተ ህዝብ መሆኑን በመጠቆም ይህንን አኩሪ ባህሉን በመጠቀም ለአከባቢው ሰላምና ለሀገራችን አንድነት የበኩሉን ሚና መጫወት ይኖርበታል ብለዋል፡፡


የሲዳማ ህዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ሆኖ የቆየው ክልል ሆኖ የመደራጀት ፍላጐት ህገ-መንግስቱ በሚፈቅደዉ መሠረት በቅርቡ በዞኑ ምክር ቤት ፀድቆ ለክልሉ ምክር ቤት መቅረቡን አስታውሰው ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ የዞኑ አስተዳደር ጉዳዩን በባለቤትነት እንደሚከታተልና አስፈላጊና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህዝቡ የመስጠት ስራን በኃላፊነት እንደሚወጣ ዋና አስተዳዳሪው በመግለጫቸው አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡


ይህ በእንዲህ እንዳለ የህዝብን ፍላጐት መሠረት ባደረገ መልኩ ኅብረተሰቡ በቅርበት መልካም አስተዳደርና ፍትህ እንዲያገኝ ታሳቢ በማድረግ የዞንና የወረዳ መዋቅሮች እንዲጠኑ የክልሉ መንግስት ቀደም ብሎ በወሰነው ውሳኔ መሠረት በዞኑ በተለያዩ አከባቢዎች እየተደረገ ያለውን ጥናት ተከትሎ የወረዳ መዋቅር ጥናት የተጀመረው የክልል ጥያቄን ለማኮላሸት ነው ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን ጠቁመው የክልል ጥያቄው አሁን እየተሰራ ካለው ወረዳ መዋቅር ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ገልፀው ጥያቄው በህገ-መንግስቱ መሠረት የሚፈታና ምላሽ የሚያገኝ ጉዳይ መሆኑን ጨምረው ጠቁመዋል፡፡


የወረዳ መዋቅር ጥናት የራሱ መመዘኛና መስፈርት ያለውና በሌሎች ዞኖችም ቀደም ተብሎ የተጀመረ ተግባር መሆኑን ገልፀው አሁን በዞኑ ጥናት በተጀመረባቸው ቦታዎች እዚም እዛም "ወረዳ ይገባናል" በሚል የሚነሱ ጥያቄዎች መኖራቸውን በመጥቀስ ለአደረጃጀት የተቀመጠውን መመዘኛ ማዕከል ባደረገ መልኩ ብቻ የሚፈፀም መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የህዝቡ የለውጥ ፍላጐት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው ህዝባችንን በኢኮኖሚ፤በማህበራዊና በፖለቲካው መስክ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በሀገራችን የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል በሚሠራው ሥራ ላይ የዞኑ አስተዳደር ከብሔሩ ምሁራንና ወጣቶች ጋር ተቀናጅቶ በቅርበት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል፡፡


ሌላው መስተካከል ያለበትና በአጭር ጊዜ ውስጥ መታረም የሚገባው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አከባቢ ያለው አላስፈላጊ ብሮክራሲ ማብዛትና ህብረተሰቡን በቀጠሮ የማመላለስ ሁኔታ ህዝቡን የሚያበሳጭና በመንግስት ላይ አመኔታ እንዲያጣ የሚያደርግ በመሆኑ በየደረጃ ካለው ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ የማድረግ ስራ ጊዜ የማይሰጠው ተግባር እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡


በአጠቃላይ በዞኑ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን፣የመሠረተ ልማት ፍላጐቶችንና አሁን በሀገራችን እየታየ ያለውን የለውጥ ሂደት ለማስቀጠል ከህዝብ ጋር ተቀራርቦ መስራትና ለውጡን ማስቀጠል እንደሚገባ አስምረው አሁን በደረሱ በተለይ የመኸርና የትምህርት ተግባራት ላይ መረባረብ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡


ነሐሴ 3/2010

ሀ ዋ ሳ
ምንጭ 

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa