Skip to main content

የገዥው ፓርቲ ከተሞችን የማስፋፋት እቅድ ይፋ ተደረገ

ሃዋሳ ከተማ እኣኣ 2003

ሃዋሳ ከተማ እኣኣ 2014

የኢትዮጵያ ከተሞችን አቅምና ቁጥርን ለማሳደግ የሚያስችል እቅድ ይፋ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ከተሞች አቅምና ቁጥርን ለማሳደግ የሚያስችል እቅድ ይፋ ተደረገ
እቅዱ በከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽንና በአለም ባንክ የስታስቲክስ ኤጀንሲ በጋራ የተሰራ ነው።
በሁለተኛው የእድገትና ትርንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን ከተሞችን ለኗሪዎች ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በመድረ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉትም ጥናቱ የሌሎች ሀገራት ምርጥ ተሞክሮዎችን ሀገሪቱ እንድታይ ለማድረግ መሞከሩ የሚመሰገን ነው።
አክለውም በተለይ በዚህ ወቅት ሀገሪቱ 2ኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እያዘጋጀት ባለችበት ወቅት መሆኑ ደግሞ ያላየቻቸው ነገሮች ካሉ እንድታይ ያግዛታል ያሉት።
ኢትዮዽያን እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2025 መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ የሚደረገው ጥረት  ከተሞችን በማሳደግና ቁጥራቸውን በማብዛት መደገፍ እንዳለበት ዛሬ የአለም ባንክ ይፋ ያደረገው ጥናት ይናገራል።
የበርካታ የሀገራችን ከተሞች ፈተና የሆነው የመሰረተ ልማት ችግር፤ የሃይልና የመብራት እጥረት፤ ዘመናዊ የደረቅና የፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርአት መስተካከል እንዳለበት የመኖሪያ ቤትና የስራ እድል ፈጠራው ላይም ሊታሰብበት እንደሚገባ ይጠቁማል።
ከዚህ አንጻር የከተሞቹ እድገት ከመምጣቱ በፊትና ከተሞቹን ዝግጁ ከማድረግ አንጻር ምን መሰራት እንዳለበት ጥናቱ የሚጠቁም መሆኑን ነው በአለም ባንክ ከፍተኛ የከተማ ልማት ኤክስፐርት አቶ አበባው አለማየሁ የተናገሩት።
ጥናቱ ሀገሪቱ ከተሞችን ለማሳደግ የሰጠችው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ያሳያል።
ይሁን እንጂ በርካታ 2ኛ ደረጃ ከተማዎችን መፍጠርና ትናንሽ ከተሞችን አቅም ማሳደግ ላይ የበለጠ ትኩረት መስጠትም ግድ ይላል።
በአዲስ አበባም እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ የሚሰራው ስራ ትክክለኛ ቢሆንም ጥናቱ የሚሰሩት ስራዎች ከከተማዋ የወደፊት የእድገት ፍላጎት ጋር እንዲመጣጠኑ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታው ተናግረዋል።
በተጨማሪም አቶ አባተ እንደሚሉት ከተሞችን በአግባቡ ለመምራት ምን አይነት የሰው ሃይል እንደሚያስፈልግ መገንዘብ ያስፈልጋል።
እያንዳንዱ ከተማም ያለውን ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ሀብት በማጥናት ከተሞች ያላቸውን ምቹ አጋጣሚ  ተጠቅመው ማደግ የሚችሉበትን መንገድ ማመቻቸት ያስፈልጋል። 
የግብርናና የኢንዱስትሪ ቀጣናዎችን በየከተሞቹ ማዘጋጀትም እንዲሁ።
የከተሞችን አቅም ለማሳደግና ከተሞችን ለማስፋፈት እንደ ትልቅ ማነቆ ከሆኑት አንዱ ገንዘብ ነው።
ሀገሪቱ የገንዘብ አቅሟን ለማዳበር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ ከሰበሰበች አቅሙን ማዳበር ትችላለችም ብሏል ጥናቱ።
ይህንን ለማሳካት ደግሞ ከተሞች ከነዋሪዎቻቸው የሚሰበስቡትን ግብር በመሰረተ ልማት ላይ ማዋል እንደሚኖርባቸው በመጥቀስ።
ከከተሞች እድገት ጋር ተያይዞ ዋና ችግር ሆኖ የተጠቀሰው ሌላው ችግር የመኖሪያ ቤት ነው።
ከተማዋ  የቤት ፍላጎት በተጨማሪ በየአመቱ የሚፈጠረውን አዳዲስ የቤት ፍላጎት ለማርካት እየተጋች መሆኑን የከተማ ልማትቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ይናገራሉ።
ከከተሞቹ እድገት ጋር ተያይዞ የሚገጥሙ የሰለጠኑ ባለሞያዎች እጥረትን አስቀድሞ ለመፍታትም እየተስፋፉ ያሉ የስልጠና ማእከላት ሚናቸው ከፍተኛ ይሆናል።
በጥናቱ የበርካታ የአፍሪካና ሌሎች አህግራት ከተሞች ምርጥና ደካማ ተሞክሮዎች ቀርበዋል።
ከዚህ አንጻር ኢትዮዽያ በትክክለኛው መስመር ላይ መሆኗንም እንደዚሁ አመላክቷል።
ምንጭ፦  ኤፍ.ቢ.ሲ

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa