Skip to main content

ጊዜ ያልገደበው የሰላማዊ ሠልፍ ንትርክ

ጊዜ ያልገደበው የሰላማዊ ሠልፍ ንትርክተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣ ገባ ከሚሉባቸው የመንግሥት ቢሮዎች መካከል የአዲስ አበባ አስተዳደር የፈቃድና የማስታወቂያ ክፍል ዋነኛው ነው፡፡
ዓመቱ ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግበት እንደመሆኑ ፓርቲዎቹ ቢሮውን ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይበልጥ አዘውትረው እንደሚጎበኙት ይጠበቃል፡፡ በከንቲባው ጽሕፈት ቤት ሥር የሚገኘው ክፍል ዋነኛ ዓላማ ስለሰላማዊ ሠልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት የሚደነግገውን አዋጅ ቁጥር 3/1983 በአዲስ አበባ ማስፈጸም ነው፡፡
የክፍሉ መጠሪያ በራሱ ባለፉት 24 ዓመታት ሰላማዊ ሠልፍንና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባን አስመልክቶ ገዥው ፓርቲና መንግሥት በአንድ ወገን፣ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ በሌላ ወገን የሚያደርጉትን ክርክር የሚያሳይ ነው፡፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጁ ፈቃድ ሳይሆን ማስታወቅን ብቻ እንደሚያስቀምጥ ይጠቁማሉ፡፡ መንግሥት በበኩሉ በግልጽ ፈቃድ ያስፈልጋል ብሎ አይከራከር እንጂ፣ በተለያዩ መግለጫዎቹ ‘ያለፈቃድ የተደረጉ ሰላማዊ ሠልፎች’ ሲል ይጠቅሳል፡፡ ይበልጥ አተኩሮ የሚከራከረው ሰላማዊ ሠልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብት እንደሌሎች መብቶች ሁሉ ገደብ የሚደረግበት መሆኑን ነው፡፡
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ባለፈው እሑድ ለማድረግ አስቦት የነበረውና በመንግሥት እንዳይካሄድ የተከለከለው ሰላማዊ ሠልፍ፣ እንዲሁም ጥር 24 ቀን 2007 ዓ.ም. አደርገዋለሁ ያለው ሰላማዊ ሠልፍ በፓርቲውና በመንግሥት መካከል የፈጠረው አለመግባባት የዚህ ችግር አንድ ማሳያ ነው፡፡ ባለፈው ሐሙስ ጥር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አመራር እንዳልሆነ ውሳኔ የሰጠበት ቡድን ውስጥ የተካተቱት የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አሥራት አብርሃም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ፓርቲው ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ አቅዶ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ፈቃድና ማሳወቂያ ክፍል በሕጉ መሠረት ለማስታወቅ ደብዳቤ ይዘው ቢሄዱም የቢሮው ሠራተኞች አልተቀበሏቸውም፡፡ ደብዳቤውን በቢሮው ጥለው ቢሄዱም በድጋሚ በፖስታ ቤት ልከው መድረሱን እንዳረጋገጡም ይገልጻሉ፡፡ በማመልከቻቸው መሠረት መልስ ሳይሰጥ የቆየው ቢሮ ከ72 ሰዓት በኋላ ሰላማዊ ሠልፉ መከልከሉን እንደገለጸላቸው አቶ አሥራት አመልክተዋል፡፡ 
አቶ አሥራት ይኼ ዓይነት አሠራርን በመቃወም ሰላማዊ ሠልፍን ለማድረግ መሞከራቸውን ያስረዳሉ፡፡ ችግሩ በአዲስ አበባ የተባባሰ ቢሆንም በተለያዩ አካባቢዎች ተመሳሳይ መሰናክሎች እንዳሉም 
ከሳምንት በፊት ሊደረግ የነበረው ሰላማዊ ሠልፍ ‘ሕገወጥ ነው’ በሚል መንግሥት በወሰደው ውሳኔ በሠልፈኞቹና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት መከሰቱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ፓርቲው ግን በሳምንቱ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ተመሳሳይ ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ እየተዘጋጀ ነው፡፡ በአማራ ክልል በደሴ ከተማ ለሚደረገው ሰላማዊ ሠልፍ ፈቃድ ማግኘቱን የገለጸው አንድነት፣ ለአዲስ አበባው ግን በአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ምክንያት ማካሄድ አትችልም መባሉን አስታውቋል፡፡ ‹‹ጥር 18 ቀን 2007 ዓ.ም. ደብዳቤ አስገብተናል፡፡ በማግሥቱ የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ስላለ አትችሉም የሚል መልስ ተሰጥቶናል፡፡ እኛም የመከልከል ሥልጣን እንደሌላቸው ገልጸን ጥር 20 ቀን ደብደቤ ጽፈናል፤›› ያሉት አቶ አሥራት፣ ሰላማዊ ሠልፉን በዕቅዱ መሠረት እንደሚገፉበት ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ከብሔራዊ ቦርድ ውሳኔ በኋላ ይህ የሚቻል አይመስልም፡፡ ሠልፉን የጠራው ‘ሕገወጥ’ የተባለው አመራር ነው፡፡ 
ይህንን መሰል ክርክር በሌሎች ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችና በመንግሥት መካከል በተደጋጋሚ ተደርገዋል፡፡ ለአብነትም መድረክ፣ ሰማያዊና ኢዴፓን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በርካታ የፖለቲካ ተንታኞችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ግጭቶቹና አለመግባባቶቹ የተከሰቱት በሕጉ መንፈስና በመንግሥት አተረጓጎም መካከል ልዩነት በመከሰቱ እንደሆነ ይከራከራሉ፡፡ ሌሎች ግን በኢትዮጵያ ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ያለው ችግር ምንጭ በሕጉ ላይ ባለው አለመግባባትና የአተረጓጎም ልዩነት የተገደበ እንዳልሆነ ያብራራሉ፡፡ 

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa