Skip to main content

የስምጥ ሸለቆ ሐይቆች ተፋሰስ ባለስልጣን ችግሮቹን ቀርፎ ወደ ተግባር በመሸጋገር አገራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ተባለ

የስምጥ ሸለቆ ሐይቆች ተፋሰስ ባለስልጣን በአጭር ጊዜ ወደ ስራ በመግባት የተጣለበትን አገራዊ ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ።
ምክር ቤቱ ማሳሰቢያውን የሰጠው በምክር ቤቱ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምጥ ሸለቆ ሐይቆች ተፋሰስና የአዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣናት የ6 ወራት የዕቅድ አፈፃፀማቸውን ዛሬ በገመገመበት ወቅት ነው።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ገመዳ ብነግዴ የባለስልን መስሪያ ቤቱን አስመልክተው በሰጡት ማሳሰቢያ መስሪያ ቤቱ  ከተቋቋመ አንድ  ዓመት ቢሞላውም አስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ አለመግባቱና በአጭር ጊዜ ወደ ስራ  በመግባት የተጣለበትን አገራዊ ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል።
እነዚህ ተፋሰሶች አሳሳቢ በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኙና ባለስልጣኑ ከሌሎች የተፋሰስ ልማት ስራዎች ልምድ በመቀመር ፈጥኖ ተፋሰሶቹ ከአደጋው ሊታደጋቸው እንደሚገባ ጠይቀዋል።
የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርም በተፋሰስ ልማት ላይ የተሰማሩ መስሪያ ቤቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንዳለበት ነው ቋሚ ኮሚቴው ያሳሰበው።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ከበደ ከንቹላ መስሪያ ቤቱ በተሟላ መልኩ ወደ ተግባር አለመሸጋገሩን በሚመለከት ለቋሚ ኮሚቴው በሰጡት ምላሽ ለዘርፉ የሚመጥኑ ባለሙያዎች ባለማግኘቱ የተሟላ የሰው ኃይል ባለመኖሩ መሆኑን አስረድቷል።
በተመሳሳይ ቋሚ ኮሚቴው የአዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣን የ6 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ላይ ግምገማ አድርጓል።
ባለስልጣኑ በረጅም ዓመታት ያካበተውን የተፋሰስ ልማት ልምድ አዳዲስ ለሚቋቋሙ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ሞዴል በመሆን ልምዱን ሊያካፍል ይገባል ብሏል።
ባለስልጣኑ በውሃ አስተዳደር የመረጃ ቋት በማደራጀትያከናወናቸው ስራዎች ቋሚ ኮሚቴው በጥንካሬ ጎኑ ገምግሞታል።
በተለይ ባለስልጣኑ ከሌሎች ተቋማት ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆነውን በሰቃ ኃይቅ ለመከላከል ያከናወናቸው ስራዎችና ውሃን ለልማት ለማዋል ያደረጋቸው ጥረቶች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ቋሚ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡
ይህ እንዳለ ሆኖ ቋሚ ኮሚቴው በባለስልጣኑ አጠቃላይ አፈፃፀም በሰጠው አስተያየት አፈፃፀሙ ከ75 በመቶ በታች በመሆኑ ዝቅተኛ በሚባል ደረጃ ላይ መሆኑን አስቀምጧል።
ለዚህም ባለስልጣኑ በውሃ አስተዳደር ፣በላይኛው ተፋሰስ የተሰጠው ትኩረት አናሳ መሆኑና፣ የበጀት አጠቃቀሙም ዝቅተኛ መሆኑን ቋሚ ኮሚቴ
ገምግሟል።
በተለይ በታችኛው አዋሽ የተፋሰስ ልማት የሚደረገውን የጎርፍ አደጋ መከላከል ስራ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም ቋሚ ኮሚቴው ገልጿል።
ያም ሆኖ አፈፃፀሙ ከእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ አንፃር ሲገመገም  የባለስልጣኑ አፈፃፀም ከእቅዱ ጋር የተጣጣመ መሆኑንና መስሪያ ቤቱ ይህንን ዘላቂ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት ነው ቋሚ ኮሚቴው ያብራራው።
- See more at: www.ena.gov.et

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa