Skip to main content

የቀድሞ ሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን (SDC) እህት የልማት ድርጅቶች የት ደረሱ?



  • የሲዳማ ዞን መንግስት በቀድሞ የሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን እህት የልማት ድርጅቶች ላይ በያዘው የተሳሳተ ኣቋም ድርጅቶቹን ኣጠናክሮ ለታለሙለት ኣላማ እንድውሉ እና ስፊውን የሲዳማን ህዝብ እንድጠቅሙ ከማድረግ ይልቅ ድርጅቶቹን እንደጠላት ንብረት በማየት የሚጠፉበትን እና የሚበተኑበትን ሁኔታዎችን ብቻ በማመቻቸት ላይ የተጠመዷል
  • የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ የመንግስት ድጋፍ ያስፈልገዋል
ክፍል ሁለት
የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ ተቋም (SMFI) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የስራ ፋቃድ ኣግኝቶ በራሱ ቦርድ የሚተዳደር የገንዘብ ተቋም ነው።ተቋሙ በከተሞች ኣካባቢ ቤትን እና ሌሎች ንብረቶችን በመያዝ ብድር የመስጠት ኣገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን፤ እንደሌሎች መሰል የኣገሪቱ የብድር እና የቁጠባ ተቋማት ሁሉ ሰዎች በቡድን ተደራጅተው ገንዘብ የሚበደሩበትን መንገዶች በማመቻቸት ኣገልግሎት ይሰጣል።
በኣገልግሎቱም እስከ ሃምሳ ሺ ነው የሚያበድር ሲሆን በግለሰብ ደረጃ ግን ከሶስት ሺ ብር በላይ ኣያበድርም። ለነገሩ በኣሁኑ ወቅት በኣገሪቱ ባለው የኑሮ ውድነት ብድሩን የሚወስዱ ሰዎች በሶስት ሺ ብር ምን ኣይነት ኢንቨስትመንት ልያደርጉ እንደምችሉ ግልጽ ባይሆንም ብዙዎቹ በገንዘብ ኣያያዝ ላይ ትምህርት ሳይሰጣቸው የብድሩ ተጠቃሚ ስለምሆኑ የተበደሩትን ገንዘብ ላላለሙለት ጉዳይ ላይ በማዋል እዳ ውስጥ ስገቡ ታይተዋል። ሰዎች የተበረሩትን ገንዘብ በውቅቱ ኣለመመለሳቸው ከብድር እና ቁጠባ ተቋሙ ጋር እንድካሰሱ ምክንያት ሆኗል። ጉዳዮቻቸው በፍርድ ቤቶች እየታየ ያሉ እና ቤት ንብረቶቻቸውን ሽጠው ለመክፈል የተገደዱ ብዙዎች ናቸው። ለማንኛውን ተቋሙ በኣሁኑ ጊዜ የብድር እና የቁጠባ ኣገልግሎትን በተዳከመ መልኩ በመስራት ላይ ይገኛል።
ለሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ የብድር እና የቁጠባ ተቋም መዳከም ምክንያቱ ምንድነው ብለን ስንል በዞኑ መንግስት ትኩረት መነፈጉ እና በሃላፊትን እና በብቃት የምመራውን ኣካል ማጣቱ ብሎም የሰለጠነ የሰው ኃይል እና የፋይናንስ ኣቅም ውስን መሆን እንደምክንያት ይነሳሉ።
የሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ዘገባ እንደምያመለክተው፤ የሲዳማ ኣርሶ ኣደሮች ከብድር እና ቁጠባ ተቋሙ ገንዘብ እንደፈለጉ እንዳይበደሩ በተበደሩት ገንዘብ ላይ ከፍተኛ የሆነና በየትኛውን ኣገር ተሰምቶ የማይታወቅ ኢንተረስት ወይም ወለድ ማለትም 18 ከመቶ እንድከፍሉ ይጠየቃሉ። ይህንን ከፍተኛ ወለድ ላልመክፈል ስሉም ሌላ ኣማራጨ የብድር ኣገልግሎቱ ሰጭ ተቋም እንድመርጡ ኣድርጓቸዋል። በዞኑ ውስጥ ያሉት ገንዝብ የመበደር ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች ከሲዳማ ማክሮፋይናንስ ተቋም ከመበደር ይልቅ ከኦሞ ማክሮ ፋይናንስ መበደርን እንደምመርጡ ሆኗል ማለት ነው። ይህም ከፖለቲካ ጋር የተያያዘ ከመሆኑ በላይ በኣገሪቱ ገዥው ፓርቲ በተለይ ወጣቶችን ኣደራጅቶ የራሱን ፖለቲካ ማራመጃነት ለመጠቀም ሲል የሚያመቻቸውን የብድር ኣገልግሎት በኦሞ ማክሮ ፋይናንስ በኩል እንድሰጥ ስለምደረገ የሲዳማ ማክሮፋይናንስ የገንዘብ ኣቅሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወረደ መጥቷል። በተጨማሪም የሲዳማ ማክሮፋይናንስ ተቋም በራሱ ብድር ለመስጠት የምጠቀመውን ገንዘብ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚበደር በመሆኑ እና ተቋሙ ያበደራቸው ግለሰቦች የወሰዱትን ገንዘብ በወቅቱ ካለመመለሳቸ ጋር የያይዞ ተቋሙ በራሱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር የማግኘት እድል ጠቧል፤ ይህም ተቋሙ ለብድር ፈላጊ ደንበኞቹ ተገቢውን ኣገልግሎት እንዳይሰጥ ኣድርጎታል።
በተቃራኒው የኦሞ ማክሮ ፋይናንስ በክልል ደረጃ የተቋቋመ ተቋም በመሆኑ በሲዳማ ውስጥ ብሎም በክልሉ ጠንካራ የብድር እና የቁጠባ ኣገልግሎት በመሰጠት ላይ ይገኛል። በተለይ በሲዳማ ዞን ውስጥ cash crop ማለትም ቡና፤ ጫት እና እህል ባለባቸው ወረዳዎች በምገኙ በእያንዳንዳቸው ቀበሌያት ውስጥ LOAN OFFICER በመቅጠር የብድር እና የቁጠባ ኣገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆኑ ይህም የሲዳማ ማክሮፋይናንስ በዞኑ ውስጥ የነበረውን የብድር እና ቁጠባ ገበያ ለኦሞ ማክሮፋይናንስ እንድያጣ ሆኗል።
የክልሉ መንግስትም ብሆን የወጣቶች entrepreneurship ፕሮግራሙ የሚሆን ገንዘብ በኦሞ ማክሮ ፋይናንስ በኩል እንድገባ እና እንድወጣ ኣድርገዋል።በተጨማሪም ከኦሞ ማክሮፋይናንስ የሚበደሩ ስዎች 10 ከመቶ ብቻ ወለድ እንድከፍሉ ስለምጠየቁ በርካታ የኣገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ኦሞ ማክሮ ፋይናንስን እንድመርጡ ምክንያት ሆኗል። ከዚህም ባለፈ ኦሞ ማክሮፋይናንስ ያበደሩት ገንዘብ በወቅቱ እንድመለስላቸው ለተበዳሪዎች ተገቢ የሆነ የገንዘብ ኣያያዝ ትምህርት ስለምሰጡ ብሎም በየቀበሌያቱ ባሰማሯቸው ባለሙያዎች በኩል በተበዳርዎቹ ላይ ክትትል ስለምያደርጉ የሚያበድሩትን ገንዘብ በወቅቱ በተበዳሪዎች እንዲመለስላቸው ኣቅም ፈጥረዋል። የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች እና ካቢኔዎችም ብሆኑ በምንቀሳቀሱባቸው የሲዳማ ቀበሌያት ህዝቡ የኦሞ ማክሮፋይናንስ ኣገልግሎት ተጠቃሚ እንድሆን የመቀስቀስ ስራ ይስራሉ ተብሏል።

ልክ ኣገሪቷም የውጭ የገንዘብ ተቋማት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ በማድረግ ለኣገር ውስጥ የገንዘብ ተቋማት ከሌላ እንደምሰጡት ሁሉ፤የሲዳማ ዞን መንግስት በዞኑ ውስጥ ከኦሞ ማክሮፋይናንስ በፊት ተቋቋሞ ኣገልግሎት ይሰጥ የነበረውን የሲዳማን ማክሮፋይናንስ ተቋም በማጠናከር በዞኑ ውስጥ ሌላ ማይክሮፋይናንስ የብድር እና የቁጠባ ኣገልግሎት እንዳይሰጥ በማድረግ የዞኑ ህዝብ ንብረት የሆነውን የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ የብድር እና የቁጠባ ተቋም ከማጠናከር ይልቅ በማዳከሙ ላይ በመበረታቱ ለብዙ ሲዳማዎች መለያቸው እና ኩራታቸው የሆነው ተቋም ከስሮ ለመዘጋት እያመራ ነው።



የሲዳማ ዞን መንግስት በቀድሞ የሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን እህት የልማት ድርጅቶች ላይ በያዘው የተሳሳተ ኣቋም ድርጅቶቹን ኣጠናክሮ ለታለሙለት ኣላማ እንድውሉ እና ስፊውን የሲዳማን ህዝብ እንድጠቅሙ ከማድረግ ድርጅቶቹን እንደጠላት ንብረት በማየት የምጠፉበትን እና የምበተኑበትን ሁኔታዎችን ብቻ በማመቻቸት ላይ የተጠመደ ይመስላል። ነገር ግን ድርጅቶቹ የሰፊው የሲዳማ ህዝብ ንብረት መሆናቸውን በመገንዘብ በሰው ኃይል እና በገንዘብ የምጠከሩበትን መንገድ ቢያመቻች መልካም ነው።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa