Skip to main content

አምራቹ በቡና ዋጋ መቀነስ እንዳይጎዳ ማድረግ ያስፈልጋል

 ...ይህ በሲዳማ ቡና አምራቾች ላይ የተከሰተው ችግር የቡና ዋጋ በዓለም ገበያ ዋጋ የሚወሰን ከመሆኑ አኳያ የሌሎች ሀገሮች ቡና አምራች አርሶ አደሮችም ችግር ነው። ችግሩ ከቡና ጋር የጠበቀ ግንኙነት ላለውና ቡና ምግቡ፣ ልብሱ፣ መዝናኛው በአጠቃላይ የኑሮው ዋልታና ማገር ለሆነው የኢትዮጵያ ቡና አምራች ምን ያህል አሳሳቢ ሊሆን እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።
የቡና ዋጋ እየቀነሰ መምጣት በአስቸኳይ የሚፈታ ካልሆነ የቡና አምራቾች የልፋታቸውን ዋጋ ወደ ሚያስገኙላቸው ዘርፎች ፊታቸውን እንዲያዞሩ የሚያስገድድ ሁኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል፤ የግብይት ህብረት ሥራ ማህበራትም ይህንኑ ስጋት እያረጋገጡ ናቸው። ሀገሪቱም ከቡና በከፍተኛ ደረጃ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ እንዲቀንስ የሚያደርግም ይሆናል። ችግሩ በቡና ልማቱና ግብይቱ ሰንሰለት የሚሳተፈውን በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ኑሮ እንዲናጋ ያደርጋል።

ኢትዮጵያ ለቡና ልማት በሰጠችው ትኩረት በቡና ተክል የተሸፈነው መሬትም ሆነ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል። ቡና ከሚመረትባቸው ክልሎች በተጨማሪ በአማራና በትግራይ ክልሎች ጭምር ቡናን በማምረት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው። ለቡና አምራቾች ወሳኝ ግብዓቶችን በማቅረብ ጭምር ድጋፍ እየተደረገ ነው።
አርሶ አደሩ ምርቱን በአቅራቢያው ለሚገኙ የራሱ የህብረት ሥራ ማህበራት እንዲያቀርብ የሚያስችል ሁኔታ በመፈጠሩም ምርቱ የደላሎችና ህገወጥ ነጋዴዎች ያለአግባብ መጠቀሚያ ከመሆን እየዳነ ነው። በአሁኑ ወቅት የቡና ግብይት የሚካሄድባቸው በርካታ የግብይት ማዕከላት ተቋቁመው እየሰሩ ናቸው። በተለይ አርሶ አደሩ ምርቱን ለህብረት ሥራ ማህበራት ማቅረብ በመቻሉ የቡና ዋጋ በሚወድቅበት ወቅት ምርቱን የሚያደርግበት እንዳያጣ የሚያስችሉት ሁኔታዎች ተፈጥረዋል። በአብዛኛው በአውሮፓ ገበያ ተወስኖ የቆየው የቡና ግብይትም ወደ እስያ ሀገሮች እንዲገባ በመደረጉ ባለፈው ዓመት ከደቡብ ኮሪያ ብቻ ከ200 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
2004 በጀት ዓመት169ሺ ቶን የታጠበና ደረቅ ቡና ወደ ውጭ በመላክ 832ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። በ2005በጀት ዓመትም ካለፈው ዓመት በ30ቶን ብልጫ ያለው ቡና ለዓለም ገበያ አቅርባለች። በቡና ዋጋ መቀነስ ሳቢያ ከእዚህ አቅርቦት740ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው ገቢ ያገኘችው።
ምንም እንኳ ሀገሪቷ ወደ ውጭ የምትልከው የቡና ምርትም በየዓመቱ ቢጨምርም በዓለም የተከሰተውን የኢኮኖሚ ቀውስ ተከትሎ የቡና ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መጥቷል። በዚህም ሀገሪቱም ሆነች ቡና አምራቹም ለተጎጂነት መዳረጋቸውን የተጠቀሰው መረጃ ያስገነዝባል ።
የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል የሲዳማ ዞን አርሶ አደሮችንና የግብይትና ህብረት ሥራ ማህበራትን ዋቢ ያደረገው የትናንቱ ዘገባችን እንደሚያመለክተውም፣ በዓለም የተከሰተውን የኢኮኖሚ ቀውስ ተከትሎ የገዥ ፍላጎት መቀዛቀዝ በመፈጠሩ ሳቢያ የቡና ዋጋ እያሽቆለቆለ መምጣት የቡና አምራቹን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳው ነው። የዞኑ ቡና አምራች አርሶ አደሮች የልፋታቸውን ያህል ተጠቃሚ እየሆኑ አይደለም። አርሶ አደሮቹ ከሁለት ዓመት በፊት አንድ ኪሎ እሸት ቡና ቢያንስ እስከ 13 ብር ይሸጡ ከነበረበት ሁኔታ ባለፈውና በተያዘው ዓመታት ዋጋው እያሽቆለቆለ መጥቶ አንድ ኪሎ እሸት ቡና በአምስት ብር ለመሸጥ ተገደዋል።
ይህ በሲዳማ ቡና አምራቾች ላይ የተከሰተው ችግር የቡና ዋጋ በዓለም ገበያ ዋጋ የሚወሰን ከመሆኑ አኳያ የሌሎች ሀገሮች ቡና አምራች አርሶ አደሮችም ችግር ነው። ችግሩ ከቡና ጋር የጠበቀ ግንኙነት ላለውና ቡና ምግቡ፣ ልብሱ፣ መዝናኛው በአጠቃላይ የኑሮው ዋልታና ማገር ለሆነው የኢትዮጵያ ቡና አምራች ምን ያህል አሳሳቢ ሊሆን እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።
የቡና ዋጋ እየቀነሰ መምጣት በአስቸኳይ የሚፈታ ካልሆነ የቡና አምራቾች የልፋታቸውን ዋጋ ወደ ሚያስገኙላቸው ዘርፎች ፊታቸውን እንዲያዞሩ የሚያስገድድ ሁኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል፤ የግብይት ህብረት ሥራ ማህበራትም ይህንኑ ስጋት እያረጋገጡ ናቸው። ሀገሪቱም ከቡና በከፍተኛ ደረጃ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ እንዲቀንስ የሚያደርግም ይሆናል። ችግሩ በቡና ልማቱና ግብይቱ ሰንሰለት የሚሳተፈውን በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ኑሮ እንዲናጋ ያደርጋል።
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የቡና አምራቹ የልፋቱን እንዲያገኝ ለማድረግ እስከአሁን የተከናወኑ ተግባሮች ውጤታማ ቢሆኑም፣ ልማቱና ግብይቱ አርሶ አደሩንና ሀገሪቷን ተጠቃሚ እንዲያደርግ የሚከናወኑ ሥራዎች ቀጣይነት እንደሚገባ ይህ በዋጋ ላይ የተከሰተው ችግር ያስገነዝባል። በተለይ በዓለም የቡና ገበያ ላይ ሰፊና ዘላቂነት ያለው ሥራ መስራት እንደሚያስፈልግ የአርሶ አደሮቹ ጥሪ ማረጋገጫ ነው።
አሁን የአርሶ አደሩንና የሀገሪቷን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመፍትሔነት የተቀመጡት ሥራዎች አርሶ አደሮች የቡና ምርታቸውን እንዲያሳድጉ፣ ቡናን ለገበያ የሚያቀርቡ አካላት እሴት ጨምረው እንዲያቀርቡ የሚያስችሉ ተግባሮችን በስፋት ማከናወን ነው። የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋትና በምርት ጥራት ላይ መሥራትም ሌሎች ወቅቱ የሚጠይቃቸው ሥራዎች ናቸው።
አርሶ አደሩ በሄክታር የሚያመርተውን ምርት ለማሳደግ የሚያስችሉ ውጤታማ ተሞክሮዎችን ማስፋት ያስፈልጋል። ለዚህም በደቡብ ክልል ከፋ፣ ሸካና ቤንች ማጂ ዞኖች በሄክታር 20ኩንታል እየተገኘ ያለበትን ተሞክሮ በፍጥነት በሁሉም ቡና አምራች አካባቢዎች ማስፋት ጊዜ ሊሰጠው አይገባም።
ለአርሶ አደሩ ምርት በእሲያ ሀገሮች ገበያ ለማፈላለግ እንደተደረገው ውጤታማ ተግባር ያሉ ሥራዎችን በሌሎች የዓለም ክፍሎችም አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲሁም የቡናን ጥራት ለማረጋገጥ እየተካሄዱ የሚገኙትን ሥራዎች ማጠናከርም ይገባል።
አጽንኦት ሲሰጠው የቆየው በቡናን ላይ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት ያስፈልጋል፤ ይገባልም።
ከእነዚህ ሥራዎች መካከልም ለዘንድሮ የሚደርሱትን ለዘንድሮ፤ የከርሞዎቹንና ቀጣዮቹንም እንዲሁ ለይቶ በማስቀመጥ በመሥራት የቡና አምራቹን ቅስም ሊሰብር የሚችለውን የቡና ዋጋ መቀነስ የሚያካክስ ተግባር ለማከናወን ፈጥኖ መንቀሳቀስ የግድ መሆን ይኖርበታል።

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa