Skip to main content

የአውሮፓ ኅብረት የፓርላማ ቡድን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ነው አለ

-    የቃሊቲን እስር ቤት እንዳይጎበኝ መከልከሉን ገለጸ 

ለሦስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረገው የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ የሰብዓዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ በአገሪቱ ውስጥ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን አስታወቀ፡፡ ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በአስቸኳይ እንደፈቱም ጠይቋል፡፡
ከሐምሌ 8 እስከ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረገው የአውሮፓ ኅብረት የልዑካን ቡድን፣ በኢትዮጵያ የነበረውን ጉብኝት ካጠናቀቀ በኋላ ሰሞኑን በሒልተን ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነበር ይህንን የገለጸው፡፡ 

እንደ ቡድኑ ድምዳሜ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ዕንባ ጠባቂ ተቋም መቋቋማቸውና በቅርቡ የፀደቀው አገራዊ የሰብዓዊ መብት መርሐ ግብር የሚበረታታ ዕርምጃ መሆኑን ገልጾ፣ መንግሥት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየፈጸመ መሆኑን አስረድቷል፡፡ 

ከመንግሥትና ከተቃዋሚ ተወካዮች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ አካላት ጋር ሰፋ ያለ ምክክርና ውይይት ያደረገው ቡድኑ፣ በአገሪቱ ዲሞክራሲ ማበብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ የሚተመንባቸው ነፃ ሚዲያና ሲቪክ ማኅበረሰባት በከፍተኛ ደረጃ እንዳይሠሩ የተደረጉ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ፀረ ሽብረተኝነት አዋጁን ጨምሮ የአገሪቱን የፖለቲካ ድባብ አፍነው ይዘውታል ያሉዋቸው ሕጎች እንዲከለሱ ቡድኑ መንግሥትን ጠይቋል፡፡ ለዚህም በእስር ላይ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላትና ጋዜጠኞች ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው ለእስር የተዳረጉ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በአስቸኳይ እንዲፈቱ መንግሥትን ጠይቋል፡፡

እስረኞችን በመጎብኘት የመጀመርያ መረጃ ለማግኘት አቅዶ እንደነበረ ያስታወቀው ቡድኑ፣ ቃሊቲ እስር ቤትን እንዳይጎበኝና እስረኞችን እንዳያነጋግር በመንግሥት በመከልከሉ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳደረበት አስታውቋል፡፡ መንግሥት የእስረኞች አያያዝን እንዲያሻሽል ጠይቋል፡፡ በ2007 ዓ.ም. ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀውን አምስተኛውን አገር አቀፍ ምርጫ፣ መንግሥት ለዲሞክራሲያዊ መርሆች ያለውን ቁርጠኝነት ለማረጋገጥ እንደ አንድ ትልቅ አጋጣሚ እንዲጠቀምበት የመከረ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት ምርጫዎች ሲከናወኑ የገጠሙ እክሎችንም ለማስተካከል ከወዲሁ እንዲሠራ ጠይቋል፡፡ 

ቡድኑ ከአፍሪካ ኅብረት አካላት ጋር ባደረገው ምክክር ኅብረቱ ሰላምንና ፀጥታን በማረጋገጥ ረገድ ያደረገው ጥረት ያደነቀ ሲሆን፣ አባል አገሮች ለፈረሙዋቸው የሰብዓዊ መብት ሰነዶች ተግባራዊነት ምን ያህል ቁርጠኛ መሆናቸውን መከታተል እንዳለበት አስገንዝቧል፡፡ ኅብረቱ በቅርቡ ለኬንያ መሪዎች በተቆረጠው የክስ ዋራንት ምክንያት ከዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ቡድኑ ኅብረቱ ከፍርድ ቤቱ ጋር በትብብር እንዲሠራ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ 

የአውሮፓ ኅብረት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ መንግሥትን በምርጫና በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ግንባር ቀደም ወቃሽ የነበረ ቢሆንም፣ ለተወሰነ ጊዜ መግለጫ ከማውጣትና አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡  

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa