Skip to main content

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰባተኛ መደበኛ ጉባዔ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተመረጡት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አቶ ደሴ ዳልኬ ሥራቸውን በይፋ ጀመሩ

የሲዳማ ብሔር ተወላጅ የሆኑት አቶ ደሴ በቅርቡ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙት ከቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ላይ የክልሉን መንግሥት ኃላፊነት ተረክበዋል፡፡

አቶ ደሴ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ማዕከል የሆነውን የደቡብ ክልል ኃላፊነት ሲረከቡ እንደተናገሩት፣ ለሕዝቡ እኩል የልማት ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ የክልሉን ሕዝብ አንድነት ለማጠናከርና የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ እንደሚሠራ አስታውቀዋል፡፡

አዲሱ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደሴ ምንም እንኳን በክልሉ ሴክተር መሥርያ ቤቶች ከዚህ ቀደም ባይሠሩም፣ ከ1996 ዓ.ም እስከ 1998 ዓ.ም የይርጋ ዓለም ከተማ ከንቲባ፣ ከ1998 ዓ.ም እስከ 2000 ዓ.ም የሲዳማ ዞን ትምህርት መምርያ ኃላፊ፣ ከ2000 ዓ.ም እስከ 2003 ዓ.ም የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ማገልገላቸው ታውቋል፡፡ ከ2003 ዓ.ም እስከ 2005 ዓ.ም ሰኔ ወር ድረስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በመሆን የሠሩ ሲሆን፣ ከሐምሌ 6 ቀን ጀምሮ አዲሱን ኃላፊነታቸውን ተረክበዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ፋኩልቲ በባይሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በለውጥ አመራር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያገኙት አቶ ደሴ፣ በአዲሱ ሹመት የተሻለ ለውጥ ያስመዘግባሉ ተብሎ እምነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በዞን ደረጃም ሆነ በፌደራል ደረጃ የነበራቸው የሥራ አፈጻጸም ለዚህ ኃላፊነት እንዳበቃቸው በክልሉ ምክር ቤት ጉባዔ ላይ ከተሳታፉ ግለሰቦች አስተያየት ለመረዳት ተችሏል፡፡ “አቶ ደሴ በተለይ በሲዳማ ዞን አስተዳዳሪነታቸው ወቅት ባሳዩት አመራር የተነሳ ክልሉን በፍትሐዊነት ያስተዳድራሉ ተብሎ ይጠበቃል፤” ሲሉ አንድ የክልሉ ባለሥልጣን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በደቡብ ክልል ሰባተኛ ጉባዔ ላይ ከተሳታፉ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መካከል፣ የሳይንስና ቴከኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በአቶ ደሴ ላይ ትልቅ እምነት አሳድረዋል፡፡ “አዲስ ከተመረጡት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደሴ ዳልኬ ጋር ላለፉት ሁለት ዓመታት ያህል ሠርተናል፡፡ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሆነው ሳውቃቸው ጥሩ ዕውቀት ያላቸው፣ ሰው አክባሪና የሚሠሩት ጠንቅቀው የሚያውቁ እንደነበሩ እመሰክራለሁ፤” ብለዋል፡፡

ደቡብ ክልል አቶ ደሴን በማግኘቱ ዕድለኛ ነው የሚሉት ዶ/ር አሸብር ምክንያታቸውን ሲያስረዱ፣ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ስብስብ በሆነው ፓርላማ በነበራቸው ግንኙነት የሥራ ባልደረባና አጋር ሆነው ነበር ያሳለፉት፡፡ ከዚህ አኳያ የሲዳማ ብሔር አባል ቢሆኑም፣ ከዚህ ቀደም አቶ ዓባይ ፀሐዬ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን እንደገለጹት አቶ ደሴም ስልጤ፣ ጉራጌ፣ ወላይታ፣ ካፋ፣ ጋሞ፣ ወዘተ ናቸው፡፡ ምክንያቱም እሳቸውም በዚያ ዓይነቱ መንገድ የተቀረፁ ናቸውና፡፡ ሁሉንም ብሔረሰቦች በእከኩልነት የሚያዩና ሁሉንም እንደራሳቸው ብሔር አድርገው ማየት የሚችሉ ሰፊና ምሉዕ ሰው ናቸው፤” በማለት ገልጸዋቸዋል፡፡

ዶ/ር አሸብር ቀድሞ ሲል በነበሩት ርዕሰ መስተዳድር የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በአቶ ደሴ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ፣ የራሳቸውንም ራዕይና ፕሮግራም ተግባራዊ እንደሚያደርጉ እምነት እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡ በዚህም በአጠቃላይ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ የዕድገትና ትራንስፎሜሽን ዕቅዱን እንደሚያሳኩ ጥርጥር አይኖረውም ብለው፣ “ከምርጫው እነደተረዳሁትና የጉባዔውንም መንፈስ እንዳየሁት የሁሉም ሰው እምነት ይኼ ነው፤” በማለት አስተያየታቸውን አጠናቅረዋል፡፡

በሐዋሳ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የክልሉ ሴክተር መሥሪያ ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎችም ኢሕአዴግ አቶ ደሴን ለዚህ ኃላፊነት በማቅረቡ ምርጫው ትክክል ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ የክልሉን ሕዝብ አንድነት ለማጠናከር የተሻለ ግንዛቤና ተነሳሽነት ያላቸው ናቸው ሲሉም ገልጸዋቸዋል፡፡

አቶ ደሴ ሥራቸውን በይፋ ሲጀምሩ እንደተናገሩት፣ በተያዘው የበጀት ዓመት በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝልማት ዘርፍ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ከ200 ሺሕ በላይ ዜጐች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ትኩረት ሰጥተው ይሠራሉ፡፡ በክልሉ በሚገኙ 14 ዞኖችና አራት ልዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ዜጐች ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa