Skip to main content

ሃዋሳን ጨምሮ “አንድነት” በህዝብ ጥያቄ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍና ስብሰባ እጠራለሁ አለ

ባለፈው ሳምንት በጐንደርና በደሴ ሠላማዊ ሰልፍ ያካሄደው አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ተመሳሳይ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለማካሄድ ከበርካታ ከተሞች የህዝብ ጥያቄ እንደቀረበለት በመጥቀስ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፉንና ህዝባዊ ስብሰባዎች ለማካሄድ እንደወሰነ ገለፁ፡፡ በአዲስ አበባ ሐምሌ 28 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ታቅዶ እንደነበር የተናገሩት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ ከጐንደርና ከደሴ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር ተመሳሳይ ሰልፍ ለማካሄድ ከተለያዩ የኦሮሚያና የደቡብ አካባቢዎች ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄ ስለቀረበለት ፓርቲው አዲስ ፕሮግራም ለማውጣት እንደወሰነ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባውን ለማዘግየትና መስከረም 5 ቀን 2006 ለማድረግ እንደታሰበ ነግረውናል፡፡
በደቡብ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ እና በሀረሪ ክልሎች ተከታታይ ሠላማዊ ሠልፎችና የአደባባይ ስብሰባዎችን ለማካሄድ ፓርቲው ወስኗል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ የአዲስ አበባው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መስከረም ተራዝሟል ብለዋል፡፡ ይሁንና ፓርቲው በአዲስ አበባ በቀጣዮቹ ሦስት ሳምንታት የአደባባይ ወይም የአዳራሽ ስብሰባዎችን ይጠራል ተብሏል፡፡ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ሐሙስ እለት ተወያይቶ መርሃግብር እንዳዘጋጀ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ በ16 ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ ስብሰባ የሚካሄደው ከሐምሌ 28 ጀምሮ ነው ተብሏል፡፡ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭና በባህርዳር ሠላማዊ ሰልፍ በሚካሄድበት በዚሁ እለት፣ በወላይታና በመቀሌ የአደባባይ ስብሰባ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ ነሐሴ 12 ቀን፣ በወሊሶ፣ በናዝሬት፣ በፍቼ እና በባሌ ሠላማዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ ነሐሴ 26 በድሬዳዋ እና በጋምቤላ የአደባባይ ስብሰባ እንዲሁም በአሶሳ ሰላማዊ ሰልፍ ይኖራል ብለዋል፡፡
በአምቦ፣ በሃዋሳ እና በደብረ ማርቆስ ከተሞችም ነሐሴ ውስጥ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደሚዘጋጁ ፓርቲው ገልጿል፡፡ የሠላማዊ ሰልፎቹና የአደባባይ ስብሰባዎቹ ዋና ዋና ትኩረቶች፣ የፀረ ሽብር አዋጁ ይሰረዝ፣ የኑሮ ውድነትና ስራ አጥነት ይቀረፍ፣ የንግዱ ማህበረሰብ ላይ ያለው ጫና ይቃለል፣ የዜጐች መፈናቀል ይቁም የሚሉ ናቸው ብለዋል - አቶ ዳንኤል፡፡ በደሴና በጐንደር ሰልፎች ላይ ህብረተሰቡ የራሱን ችግሮችም በመፈክር መግለፁን አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ ከሃይማኖት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች መቅረባቸውንም ተናግረዋል፡፡ የፓርቲው የሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ንቅናቄ መስከረም 5 ቀን በአዲስ አበባ በሚካሄደው መርሃ ግብር እንደሚጠናቀቅ ከገለፁ በኋላ ፣ መስከረም 30 በፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጡ አዳዲስ አመራሮች ቀጣይ የፓርቲውን እንቅስቃሴ ይወስናሉ ብለዋል - አቶ ዳንኤል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa