አዋሳ ሚያዚያ 15/2005 በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በሌኩ ከተማ በሀገ ወጥ መንገድ በከተማው የሚሸጡ መድሃኒቶች መበራከት አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን የከተማው ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በከተማው በገበያ ፣በመንገድ ዳርና ሱቆች በህገ ወጥ መንገድ የሚሸጡ መድሃኒቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መቷል፡፡ ይህም ለነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሪፖርተር አስተያየታቸውን የሰጡ አንዳንድ የከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ከነዋሪዎቹ መካከል ወይዜሮ ጥሩወርቅ ወልዴ፣ ወይዜሮ አበባው በቀለና ወይዘሮ ምትኬ ጫኒያለው እንዳሉት በተለይ ረቡዕና ቅዳሜ መድሃኒቱ ገበያ ላይ እንደማንኛውም ሸቀጥ ቀርቦ እየተሸጠ ይገኛል፡፡ መድሃኒቱ የሚሸጠው ምንም ስለመድሃኒቱ ዕውቀት በሌላቸው ግለሰቦች መሆኑ ጉዳዩን እጅግ አሳሳቢ እድሮጎታል፡፡ በተለይ የሰው መድሃኒት ከከብቶች፣ ከበግና ከፍየል በድሃኒቶች ጋር አንድ ላይ ተቀላቅሎ መሸጡ የነገሩን አሳሳቢነት በህብረተሰቡ ዘንድ እንዲጨምር ማድረጉን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡ የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ቡርሶ ቡላሾ ነዋሪዎች ያነሱት ቅሬታ ትክክል መሆኑን በማመን ችግሩን ሙሉ ለሙሉ ለማስወገድ ከወረዳ አስተዳደር፣ ከፖሊስና ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ህገ ወጥ መድሃኒቶቹ ጎረቤት ወረዳዎችና ዞኖች በማቋረጥ ወደ ከተማ የሚገቡ ስለሆነ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከአጎራባች ወረዳዎችና ዞኖች ጋር በመሆን እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመሩ ስራዎችን ከዳር ለማድረስ የህብረተሰቡ የተቀናጀ ትብብርና እገዛ ወሳኝ በመሆኑ በህገ ወጥ መንገድ በመድሃኒት ንግድ የተሰማሩ ግለሰቦችን በማጋለጥ ህብረተሰቡ እንዲተባበር ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=7329&K=1
የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል
Comments
Post a Comment