Skip to main content

ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እና ሲዳማ


ፉቄ ዲሬሞ ከሃዋሳ
የሲዳማ የራስ ገዝ የክልል ኣስተዳደርን በተመለከተ በህዝቡ ዘንድ የምነሱት ጥያቄዎች እድሜ ጠገብ ናቸው። ኣብዛኛዎች እንደምገምቱት በተለይ ከዛሬ ኣስር ኣመት ወዲህ የተጀመረና ከግዜ ወደ ጊዜ በህዝቡ ዘንድ እየሰረጸ የመጣ ጉዳይ ሳይሆን የሲዳማ ህዝብ ላለፉት ከሰላሳ ኣመታት በላይ ለነጻ ዲሞክራሲያዊ የራስ ኣስተዳደር ሲያደርግ ነበረው ትግል ኣካል ነው።

የሲዳማ ህዝብ ከማንም የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ቀደሞ ለራስ ገዝ ኣስተዳደር እና ለመልካም ኣስተዳደር ብሎም ለዲሞክራሲያዊ ስርኣት መስፈን የታገለ ህዝብ ነው። ይህም ማለት የሲዳማ ህዝብ መልካም ኣስተዳደር እና የዲሞክራሲያዊ ስርኣት ግንባታ ኣስፈላግነትን በቅጡ የተረዳ ብሎም ሲታገልለት ቆየው ህዝብ ነ፤ ለስኬቱም ብሆን ኣያሌ ውድ የሲዳማ ልጆች መስዋዕት ሆኖለታል እየሆኑም ይገኛል።

የሲዳማ የምንም ጊዜ ውድ ልጆቿ የተሰውለት የመልካም ኣስተዳደር እና ዲሞክራሲያዊ የክልል ኣስተዳደር በተለይ ከሃያ ኣመታት በፊት በሲዳማ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በመላዋ ኢትዮጵያ የነበረው የደርግ ስርኣት ተገርስሰው ኣዲስ ስርኣት ሲቋቋም እውን ሆኖ ነበር ብሆንም ከጥቂት ጊዚያት በኃላ የራስ ክልል ኣስተዳደር መብቱን እንደገና መነጠቁ ይታወሳል።

የሲዳማ ህዝብ ከመቶ ኣመታት በላይ ከሌሎች የኣገሪቱ ብሄሮች፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ጋር ተፋቅሮ፤ ተቻችሎ በኣንድነት የኖረ ህዝብ ብሆንም ፖለቲካዊ የራስ ገዝ ክልላዊ ኣስተዳደሩን መነጠቁ እና ከሌሎች ኣናሳ ብሄሮች ጋር በስሜ ደቡብ በኣንድ ክልል ውስጥ መጠፈሩን ሳይቀበለው ኖሯል።

በኢህኣዴግ የምመራው መንግስት የወሰደውን ይህንን እርምጃ በተመለከተ በወቅቱ ህዝቡ ተቃውሞውን በተለያዩ ኣጋጣሚዎች እና በተለያየ መልኩ የገለጸ ቢሆንም ሰሚ ሳያገኝ ቀርቷል። ከዚህም ባሻገር በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በራሱ ልጆች መተዳደሩ፤ በራሱ ቋንቋ የመማሪ እና የመዳኘት መብት ባለቤት መሆኑ ብሎም ኣዲስ በተመሰረተው የደቡብ ኢትዮ ጵያ ብሄሮች፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ክልላዊ ኣስተዳደር በኣስተዳደራዊ እርኬኖች ውስጥ የኣንበሳውን እጅ ማግኘቱ በወቅቱ ውስጥ ውስጡን ይቀጣጠል የነበረውን የራስ ክልል ኣስተዳደር ጥያቄ ልያስክነው ችሏል።

ነገር ግን ከግዜ ባኃላ የሲዳማ ህዝብ የራሱን ክልላዊ ኣስተዳደር መብት ኣጥቶ ከሌሎች ጋር መጠቃለሉ የኣገሪቱ ህገ መንግስት በምፈቅደው መሰረት ማግኘት ይገባው የነበራቸውን ኣያሌ መብቶቹን እንዲያጣና የሚያገኛቸውን እድሎች ብሆን ከሌላው ጋር እንዲጋር የግድ መሆኑ እና ከሌሎች ካጋጠሙት ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች መጓደል ጋር ተያይዞ ለጥቅት ጊዚያትም ብሆን ስክኖ የነበረውን የራስ ክልል ጥያቄ ኣቀጣጥሎታል።

ራስን በክልል ደረጃ የማስተዳደር ጥያቄን እንደየመጨረሻ ኣማራጭ በማስቀመጥ ሌሎች የመልካምኣስተዳደር ጥያቄዎችን ያነሳው የሲዳማ ህዝብ በመልካም ኣስተዳደር ችግሮቹ ላይ ያነሳቸውን ጥያቄዎች በተለያዩ ጊዚያት እና በተለያዩ መንገዶች በወቅቱ የኣገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት ለኣቶ መለስ ዜናዊን ጨምሮ በየደረጃ ላሉ ጉዳዩ ለምመለከታቸው መንግስታዊ ኣካላት ያቀረበ ቢሆንም በእነዚሁ መንግስታዊ ኣካላት ባለስላጣናትን ልክ እንደየማዳ ጫዋች ከቦታ ወደ ቦታ በመቀያየር የተሰጡ ምላሾች ኣጥጋቢ ኣልነበረም።

ኣነሰም በዛም ለሲዳማ ህዝብ የልማት ጭላጭል ያሳይ የነበረውን የኣቶ ኣባቴ ኪሾን ኣስተዳደር በሙሲና እና በሌሎች ጉዳዮች ሰበብ ኣስባብ ከስልጣን ላይ በማንሳት የክልሉን ርዕሰ መስተዳደሪነትን የተረከበው የኣሁኑ የኣገርቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በኣቶ ኃይለማሪያ ደሳለኝ ይመራ የነበረው የክልል ኣስተዳደር በሲዳማ ዞን ውስጥ ይከተለው በነበረው የተበላሽ የመልካም ኣስተዳደር እና ሰብኣዊ መብት ጥሰት ከህዝቡ የፍትህ እጦት ብሎም የልማት መጓደል ጋር ተያይዞ እንኳል ዘንቦብሽ ድሮም ጤዛ ነሽ እንድሉ ሆነና ህዝቡን ለኣደባባይ ኣበቃው፤ የዛሬ ኣስር ኣመት በሎቄ ጉድማሌ ተሰብሰቦ በመፍትሄዎቹ ላይ እንዲመክር ኣስገደደው።

በብዙ ሺዎች የምቀጠር ህዝብ ለቀናት የመከሩት የሲዳማ ሽማግሌዎች በሰጡት ውሳኔ መሰረት ጥያቄውን ለምመለከተው መንግስታዊ ኣካለት በሰላማዊ ስልፍ ለመቅረብ የወጣ ሲሆን የወጣው ህዝብ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በተከፈተባቸው የገዳይ ጥይት እሩምታ በመቶዎች የሚቆጠሩት ለሁለተኛ ጊዜ ለሲዳማ ህዝብ የራስ ክልል ኣስተዳደር ተሰውተዋል።

ለመቶዎች የሲዳማ ተወላጆች መገደል ብሎም በወቅቱ ለነበረው የሰብኣዊ መብት ረገጣ ዋነኛ ኣንቀሳቃሽ ሞተር ከሆኑት ግለሰቦች መካከል የወቅቱ የደቡብ ክልል ፕረዚዳንት ብሎም በኣሁኑ ጊዜ የኣገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ኣንደኛው ግንባር ቀደሙ ሲሆኑ፤ መለሰ ማሪሞ፤ በረከት ስሞኦን፤ ኣባዱላ ገመዳ እና ሌሎች ባፈሰሱት የንጽሃን ሲዳማዎች ደም በኣሁኑ ጊዜ ለከፍተኛ መንግስታዊ ስልጣን የበቁ ይገኑበታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማሪያ ደሳለኝ እና ሌሎች የወቅቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በእጃቸው የሲዳማዎች ደም ስላለባቸው ለፍርድ ቀርበው የሚገባቸውን ቅጣት ማግኘት እያለባቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ ለተሻለ ስልጣን በመታጨት እና በመሾም ላይ ናቸው።

እነ ኣቶ ኃይለማሪያም በመቶዎች የሚቆጠሩትን ሲዳማዎች በጠራራ ጸሀይ በግፊ ካስገደሉ በኃላ የሲዳማ የራስ ገዝ የክልል ኣስተዳደር ጥያቄን ኣሳንሰው ከሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ጥያቄ ደረጃ በማውረድ ለህዝቡ ያላቸውን ንቀት ኣሳይተዋል። ያስገደሏቸውን ሲዳማዎች ጸረ ስላም በማለት ተሳልቀውባቸዋል። የንቀታቸው ንቀት ለሲዳማ ህዝብ የራስ ክልል ኣስተዳደር ምላሽ የሲዳማን ደም ከማፍሰሳቸው ባሻገር የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር ከሲዳማዎች እጅ በመንጠቅ የኣገሪቱን ህገመንግስት ተጻረዋል።

ቀጥሎ ባሉት ኣመታትም በሲዳማ ዞን ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩት የልማት ድርጅቶችን በመበተን በዞኑ የነበረውን የልማት እንቅስቃሴ ኣስተጓጉለዋል የሲዳማን ኢኮኖሚያዊ ኣድቋል።

ይቀጥላል

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa