Skip to main content

ጉዳዩ፡-ስለ ፍትሕ መጓደል አስቸኳይ መፍትሔ እንድሰጠን ስለማሳሰብ ይሆናል::

ቀን፡-11/01/2005
ቁጥር፡-ድሩ ቄለ01/2005 
ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞከራሲዊ ሪፓብልክ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት 
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡-ስለ ፍትሕ መጓደል አስቸኳይ መፍትሔ እንድሰጠን ስለማሳሰብ ይሆናል::
ከላይ በመግቢያው ላይ እንደተጠቀሰው በኢትዮጵያ ፌ/ዴ/ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 9 በንዑስ አንቀጽ አንድ ላይ የበላይ ህግ ያጎናፀፋቸው መብቶች በሰላማዊ አሰራር የመንግስት አካል ወይም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ-መንግስት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደማይኖራቸው ይደነግጋል፡፡
ይህ ህገ-መንግስት እንደገና በአንቀጽ 8 በንዑስ አንቀጽ አንድ ላይ በኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የኢትዮጵያ ሉአላዊ ሥልጣን ባለቤቶች መሆናቸውን ይደነግጋል፡፡
ይሄ ሕገ-መንግሰት ከደነገገው ውጪ የደቡብ ብሔሮች በሔረሰቦችና ሕዝቦች ከልል የሚገኙ አንዳንድ ከፍተኛ አመራሮች ለሕዝብ መልካም አስተዳደርና ልማት ማረጋገጥ ካለመቻላቸውም በላይ በሕዝብና በመንግስት መካከል አመኔታ የሚሸረሽሩ ድርጊቶችን ፣ክራይ ሰብሳብነትንና ምግባረ-ብልሹነትን ለረጅም ጊዜያት ከመፈፀማቸው ጋር ተያይዘው ሕዝቡ አንቅሮ ስለተፋቸው ይህንን ለማስለወጥ የህዝቡን ብሶት የሚቀሰቅሱ አጀንዳዎችን አንስተው በሕዝቡ መካከል በመዛት ያንኑ መልሰው ለመሸንገል በሚል አጀንዳ የመንግስትን ታአማንነት ለማግኘት ስሉ የመንግስትን ውስን ሀብት ለማባከን ላይ ታች ሲሉና የሥልጣን ዕድሜ ሲያራዝሙ ቆይተዋል፡፡
በዚህም መነሻ ህገ-መንግስቱ ለሲዳማ ህዝብ ካጎናፀፈለት መብቶች አንዱ የሆነውን ባህሉን ለማሳደግ የፍቼ-ጫምባላላ በዓል ስያከብር እስከ ዛሬ ደርሷል፡፡በነቂስ የሚወጣው ህዝብም በዝህ በዓል እንደባህሉ የሚወደውን አወድሶ፣ያልተመቻቸውንና ህጋዊነቱን ያጎደለውን ነገር ወቅሶ በሰላም ወደቤቱ ይመለሳል፡፡በነሐሴ 8-9/2004ዓ.ም የዋለው የፍቼ-ጫምባላላ በዓልም በሲዳማ ዞን አስተዳደር ጋባዥነት በዓሉን አከብሮ በዋለበት ወቅት በዴሞክራሲያዊና በጨዋ ሁኔታ ከማክበሩም በተጨማሪ እንደተለመደው ባልተመቸውና ህገ-መንግስታ መብታቸውን ነክቶብናል ያለውን ወቅሶ መንግስትን ግን አሞጋግሶ ወደየቀዬያቸው በሰላም ተመልሷል፡፡ይህ ሰላማዊነት ደግሞ የሲዳማ ባህልም ስለሆነ በነቂስ የወጣው ህዝብ በዓሉን በሰላም አከብሮ ተመልሷል፡፡ ይሁንና እነዚህ የመልካም አስተዳደር ሽታ በአጠገባቸው ያላለፋቸው መንግስትንና ህዝቡን የሚያጣላ ሥራ የሚሠሩ አመራሮች በለመዱት የአምባገነንነትና የአፈና ባህርያቸው በመጠቀም ተንኮል የወለደው (አንድ ባለሥልጣን ተሰደበ በሚል) ድርሰት በመጠቀም በሰላማዊ መንገድ መደበኛ ኑሮውን እየመራ ይህች አገር ለተያያዘቸው ልማትና እድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት ደፋ ቀና የሚለውን የሲዳማ ህዝብ በፍቼ-ጫምባላላ በዓል ላይ ተገኝታችሁ የክልሉን ርዕሰ መስተዳደር የሚነካ(የሚውቅስ) ሐሳብ አንፀበርቃችኋል በሚል ሰንካላ ምከንያት ህዝቡን በአጠቃላይ በማሸበር፣የገጠርና የከተማ ነዋሪዎችን ሁሉም ይተሰራል በሚል ሽብር በመንዛት ህዝቡ መንግሥት ከተያያዘው የልማት አንቅስቃሴ ጎዳና ውጪ የማድረግ ሥራ ሲሠሩ ሰንብተዋል፡፡ከማሸበርም አልፈው የሲዳማ ብሔር አባላትን ከሽማግለዎች፣ ከተማሪዎች፣ ከነጋደዎች ከመንግሥት እና ከግል ድርጅት መሥሪያ ቤት ሰራተኞች ብዙ ሰዎችን ያለህግ አካሄድ በሁሉም ወረዳዎችና በሐዋሳ ከተማ በእስር ቤት በማጎር በመደበኛ ሥራዎቻቸው በማስተጓጎል በዚህ ኑሮ ውድነት ቤተሰቦቻቸውን የመበተን አደጋ ላይ ጥለዋል፡፡ከዚህም ባሻገር ህዝቡን በከፍተኛ ምሬት ውስጥ የመክተት ሥራ እየሠሩ በመቆየታቸው የሀገር ሽማግለዎች ከዚህ እኩይ ተግባራቸው እንድመለሱ እና ታሣሪዎቹን እንድፈቱ ብጠይቋቸውም “እኔን 18 ሚሊዮን ህዝብ የሚያስተዳድረውን ንጉስ ስሜን በክፉ ያነሱትን እበቀላቸዋለሁ፣ገና አደሄያቸዋለሁ፣በእግሬ ሥር እስክንበረክኩ ድረስ በወኂን ቤት አወርዳቸዋለሁ” እና ወ.ዘ.ተ ብሎ እስከመዛት የለየላቸው ፍፁም አምባገነን ሆነው በማስቸገራቸው በአሁኑ ሰዓት ያለክስ ታሰረው፣ እየታሰሩና እየተሸማቀቁ የሚገኙት ለአብነት ብቻ፡- 
ተ/ቁ የታሣሪው ሥም የት/ት ደረጃ የታሣሪው ሥራ የታሠረበት ቀን የእስራት ቀናት ብዛት ክሱ ያለበት ከረጃ ምርመራ
1. አቶ እያሱ ረጋሳ MA የመንግስት ሰራተኛ አልታወቀም እስካሁን ድረስ ክስ ያልተመሰረተበት ታስረው ያሉ
2. አቶ ዱካሌ ላሚሶ MA የመንግስት ሰራተኛ 10/12/2004ዓ.ም ›› ›› ታስረው ያሉ
3. አቶ አባቴ ክሞ BSc የመንግስት ሰራተኛ 11/12/2004ዓ.ም ›› ›› ታስረው ያሉ
4. አቶ ቦሾላ ጋብሶ ቀለም ነጋዴ 19/12/2004ዓ.ም ›› ›› ታስረው ያሉ
5. አቶ አዕምሮ ወናጎ የግል ድርጅት ›› ›› ታስረው ያሉ
6. አቶ ደበበ ዳንጉራ ›› ›› ታስረው ያሉ
7.. አቶ ኡጋሞ ሀናጋ BSc መንሥታዊ ያልሆኔ ድርጅት ›› ›› ታስረው ያሉ
8. አቶ ለገሠ ሀንካርሶ 10+3 መንሥታዊ ያልሆኔ ድርጅት(NGO) 01/13/2004ዓ.ም ›› ›› ታስረው ያሉ
9 ለሎችም (1000ዎች) አልታወቀም አልታወቀም አልታወቀም አልታወቀም አልታወቀም ታስረው ያሉ
እነዚህንና ሌሎችም ሲዳማ ተወላጆች ህገ-መንግሥቱ የሠጣቸው ሰብዓዊና ዴሞክራሳዊ መብቶቻቸውን ተነፍገው በዚህ ክልል የህግ በላይነትን በመፃረር እራሳቸውን ከህግ በላይ ባደረጉ አምባገነን መሪዎች የስልክ ትዕዛዝ ብቻ ፈጽሞ ህግን በተፃረረ ሁኔታ ታጉረው የሚገኙትን ንፁሐን ዘጎች የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሳዊ መንግሰት ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስቸኳይ መፍትሔ እንድሰጣቸው ጥቆማ በመስጠት የዘግነት ግዴታችንን ለመወጣት የወደደን መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ከሰላምታ ጋር
ህገ-መንግስት ይከበር!
ግልባጭ፡-
• ለኢህአዴግ ጽ/ቤት
• ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን
http://www.facebook.com/groups/289317227830513/permalink/332662266829342/

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa