Skip to main content

የሕግ ፍትህ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምን ሠራ?



ባለፈው ዕትማችን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ ፍትህ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በ2004 ዓ.ም ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ ከኮሚቴው አባል የተከበሩ አቶ ዳዊት ተፈራ ጋር ባደረግነው ቃለ ምልልስ ማስነበባችን ይታወሳል፤ በዚህ እትማችን ደግሞ ቀሪውን ክፍል ይዘን ቀርበናል፡፡ 
ሕግ ከማውጣት አንፃር ቋሚ ኮሚቴው ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ አምስት ረቂቅ አዋጆችን ከሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር በመተባበር ሰርቷል፡፡ረቂቅ ሕጎቹ የሕግ አወጣጥ ሥርዓትን በተከተለ ሁኔታ ተረቅቀው የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርት ቀርቦባቸው በምክር ቤቱ እንዲፀድቁ ተደርጓል፡፡ ሌላው ቋሚ ኮሚቴው ብቻውን የሚመለከተው እና ኃላፊነቱን ወስዶ በማርቀቅ ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ በማቅረብ የፀደቀው 'የወሳኝ ኩነት እና ብሔራዊ መታወቂያዎች' የሚለው አዋጅ ነው፡፡
በዚህ አዋጅ መሰረት የእያንዳንዱ ሰው ከልደት እስከ ሞት ያለው መረጃ ይመዘገባል፡፡ ለዚሁ ሥራ ከታች እስከ ላይ መዋቅር ያለው ጽ/ቤት ይቋቋማል፡፡ በአዋጁ መሰረትም እንደ ኢትዮጵያዊነት ለሁሉም ብሔራዊ መታወቂያ ይዘጋጃል፡፡መታወቂያው ሙሉ የማንነት መረጃን የያዘ ሲሆን ፤ለብሔራዊ ደህንነት እንዲሁም መንግሥት ሊዘረጋቸው ለሚፈልጋቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማቶች ጭምር አጋዥ ነው የሚሆነው፡፡ 
ምንም እንኳን በበቂ ሁኔታ ተሳትፎበታል ለማለት ባያስደፍርም በረቂቅ አዋጁ ላይ ሕዝቡ ተሳትፎ እንዲያደርግበት ኮሚቴው ጥረት አድርጓል የሚሉት አቶ ዳዊት ረቂቁን ለማዳበር ከሚመለከታ ቸው አካላት ጋር የውይይት መድረክ ተፈጥሮ ጠቃሚ ግብአትም ከመገኘቱም በላይ ለጉዳዩ ቅርበት አላቸው ተብሎ ለሚታሰቡ ወገኖችና ተቋማትም ረቂቁ ላይ የበኩላቸውን ሃሳቦች ሰንዝረዋል።
ሌላው ቋሚ ኮሚቴው ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ ከተለያዩ ወገኖች የሚቀርቡለትን ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን መርምሮ ተገቢው ማስተካከያ እንዲደረግ ለሚመለከተው አካል የውሳኔ ሃሳብ ማቅረብ ነው፡፡ በዚህ መሰረት በዓመቱ 123 ጥቆማዎችና አቤቱታዎችን ተቀብሏል፡፡48 የሚሆኑት ጥቆማዎችና አቤቱታዎች በመመሪያው መሰረት መፍትሄ ተስጥቷቸዋል፡፡44 ጉዳዮች ደግሞ መመሪያውን ያልተመለከቱና ምላሽ ያልተሰጣቸው ሲሆኑ ስድስት የሚሆኑት በመታየት ላይ ናቸው፡፡ ዘጠኝ ጉዳዮች ዘግይተው ስለደረሱ በቀጣይ የሚታዩ ናቸው፡፡ ከዚህ ሌላ 16 ጉዳዮች በግልባጭ ቋሚ ኮሚቴው እንዲያየው የተላኩበት ሁኔታ አለ፡፡ 
እዚህ ላይ ቋሚ ኮሚቴው የተቸገረበት ሁኔታ መኖሩን አቶ ዳዊት ይናገራሉ፡፡ « በፍርድ ቤት የታዩ እና ውሳኔ የተሰጣቸውን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴው ሊያይ አይችልም፤ነገር ግን ሕዝቡ እስከ ሰበር ድረስ የታዩ ጉዳዮችን ወደ ቋሚ ኮሚቴው ይልካል፡፡ ይህ ትክክል አይደለም፡፡ ይህን የሚያደርገው ከግንዛቤ ችግር ሊሆን ይችላል፡፡ይህ ሁኔታ ምክር ቤቱ እዚህ ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ መሥራት እንዳለበት ያሳያል» የሚሉት አቶ ዳዊት መመሪያው የማይፈ ቅዳቸውን አቤቱታዎች፣ ቅሬታዎች፣ ለቋሚ ኮሚቴው ልኮ ያልሆነ ውሳኔና ውጤት መጠበቅ፣ ተገቢ አለመሆኑንና ለአላስፈላጊ እንግልትም የሚዳርግ በመሆኑ ሕዝቡ ምን ዓይነት ጉዳይ ነው ለኮሚቴው ማድረስ አለብኝ ብሎ ራሱን መጠየቅና የሙያ ሰዎችን ማማከር እንዳለበት ይመክራሉ።
ቋሚ ኮሚቴው ሊያይ የሚችለው በፍትሕ አስተዳደር፣በፍርድ ቤቶች፣በመልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ ተጨባጭ የሆነ አድልዎ የተፈፀመ እንደሆነ፣ በሙስና ተግባር፣ በአጠቃላይ የፌዴራል ሥርዓትን ሊጎዱ የሚችሉ ሆነው በሌሎች አካላት ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ የተያዙ ጉዳዮች ሲሆኑ ነው፡፡ 
በሀገሪቱ ለፍትህ አስተዳደር እና መልካም አስተዳደር መጐልበት የሚያግዝ አሠራር ለመቀየስ በቋሚ ኮሚቴው የተያዘው ሥራ አበረታች ነው የሚል እምነት መኖሩን ነው አቶ ዳዊት የሚገ ልጹት።
በአጠቃላይ ቋሚ ኮሚቴው በዓመቱ ይዞት ከተነሳው እቅድና ተልዕኮው አንፃር ውጤታማ ሥራ ሠርቷል ማለት እንደሚቻልም አቶ ዳዊት ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ኮሚቴው የሚታዩ የአሠራር ክፍተቶችን ከሕግ ዓይን አኳያ በመጠቆም ከሌሎች አካላት ጋር በተባባሪነት ሥራውን የሚቀጥል ሲሆን፤ በ2005 ዓ.ም ደግሞ ከዚህ በተሻለ አቅምና ብቃት በመሥራት በአሠራር የሚታዩ ጥቃቅን ግድፈቶችን በማረም ቋሚ ኮሚቴው በቁርጠኝነት እንደሚሠራም ነው የገለፁት፡፡ 

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa