Skip to main content

ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕጎችን በሦስት ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተመውን ሰነድ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስረከበ፤ በሲዳማ ኣፎ መቼ ነው መሰል ሰነዶች መቶርጎም የምጀምሩት?

አዲስ አበባ መስከረም 15/2005 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች፣ ስምምነቶችና መርሆዎችን በአማርኛ፣ በኦሮምኛና በትግርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተመውን ሰነድ ዛሬ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስረከበ። ኮሚሽኑ በሁለት ሚሊዮን ብር ወጪ ያሳተማቸውን 35 ሺህ "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች አስረክበዋል። በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አዳራሽ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አምባሳደር ጥሩነህ ዜና እንደገለጹት አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች፣ ስምምነቶችና መርሆዎች በሰብአዊ መብት ማስከበር ተግባር ላይ ሳይውሉ ቆይተዋል። እንዲሁም ወደ አገር ውስጥ ቋንቋዎች ለረጅም ጊዜያት ሳይተረጎሙ መቆየታቸውንም አስታውሰዋል። ኮሚሽኑ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ህጎቹን ወደተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉመው ዳኞች እና ዐቃቤ ሕጎች ከአገሪቱ ሕጎች ጋር አቀናጅተው እንዲጠቀሙባቸው ማሳተሙን አስረድተዋል። በአገሪቱ የሰብአዊ መብት ጥሰትን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ዳኞች እና ዐቃቤ ሕጎች "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነድ በሥራ ላይ በማዋል ሊጠቀሙበት እንደሚገባም ገልጸዋል። እንዲሁም ለፌዴራልና ለክልል ሕግ አውጪ አካላት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ በሰብአዊ መብት ዙሪያ ለሚሰሩ መንግሥታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነዱን ለማሰራጨት የሚያስችል ስትራቴጂ የተነደፈ መሆኑን አመልክተዋል። "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነዱ በአፋርኛና በሶማሊኛ ቋንቋዎች በመተርጎም በክልሎቹ ለሚገኙ ዳኞች እና ዐቃቤ ሕጎች ለማዳረስ ዝግጅት መደረግ ላይ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደር ጥሩነህ በሌሎች የአገሪቱ ቋንቋዎችም ተተርጉሞ እንዲዳረስ ይደረጋል ብለዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መድኀን ኪሮስ እንዳሉት "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነድ ውጤታማ የሆነ የዳኝነት ሥራ ለመስራት የሚያግዝ ነው። ፍርድ ቤቶች የሰብአዊ መብቶችን ለማሰከበር አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕጎች፣ ስምምነቶችና መርሆዎች መሠረት በማድረግ ከሌሎች የአገሪቱ ሕጎች ጋር በማጣጣም የሚሰሩበት መሆኑንም ገልጸዋል። የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ደሞዜ ማሜ በበኩላቸው ፍርድ ቤቶች በሕግ ትርጓሜ በኩል ዓለም አቀፍ ሕጎችን በማካተት እንዲሰሩ የሚያደርግ ሰነድ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕጎች በአገር ውስጥ ቋንቋዎች ተርጉመው በዳኝነት ሥራ ላይ እንዲውል መደረጉ በአገሪቱ የሰብአዊ መብት ታሪክ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምድ መሆኑን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የዜጎችን የመብት ጥሰትን ለመከላከል ለሚያከናውናቸው ተግባራት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ደሞዜ ገልጸዋል።
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=2592

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa