Skip to main content

ይድረስ ለአቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኤፌዴሪ ምክትል ጠ/ሚ/ር ና የውጭ ጉዳይ ሚ/ር


መ/ር ቀለሙ ሁነኛው
Kelemhun@yahoo.com
አቶ ኃ/ማርያም የገፅታዎ ወዘና ሲታይ በእውነቱ
ወንበሩ የተመችዎት ይመስላል፡፡ እነ አቶ መለስ ደደቢት
በረሀ መሽገው ሲዋጉም ሆነ ደርግን ድል አርገው
ቤተመንግስት ሲገቡ ርስዎ በትግል ማህፀን ውስጥ
አልተፀነሱም ነበር፡፡ ከወቅቱ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ርቀው
ባህር ማዶ በትምህርት ላይ እንደነበሩ ወዳጄ ተመስገን
በፍትህ ጋዜጣ ላይ አስነብቦናል፡፡ መቼም እደለኛ ነዎት
ይህም ከዕድል ከተቆጠረ፤ ህወሓት /ኢህአዴግ ሕዝብን
በብሔረሰብ ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲውን በመላው
አገሪቱ ሲተገብር በወላይታ ብሔር ተወላጅነታችሁ ርስዎና
አምባሳደር ተሾመ ቶጋ የአቶ መለስ ቀኝ እጅ በመሆን ብቅ
አላችሁ፡፡ የሁለታችሁ ፍፁም ታዛዥነት ለስልጣን ማማ
አበቃችሁ፡፡
ክቡር አቶ ኃ/ማርያም የርስዎ መሰላል ግን የሚገርም
ነው፡፡ ከስልጣን ወደ ስልጣን ለመሸጋገር ከመፍጠንዎ
የሀላፊነትዎ መደራረብ ከበረሀ ጀምሮ ለ17 ዓመታት በፅናት
የታገሉት አቶ አዲሱ ለገሠና አቶ ስዩም መስፍን በተናጠል
የያዙትን የሥልጣን ቦታ ርስዎ በግልዎ ሲጠቀልሉት ምን
አይነት ደስታ ተስማዎት ይሆን? የተደራረበልዎት ሥልጣን
የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር፣ የኤፌዲሪ ም/ጠ/ሚ/ር፣
የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የሕዳሴ ግድብ አስተባባሪ ብሔራዊ
ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ የ. . .ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ . . .
አቤት የስልጣንዎ ብዛት! መቼም ስልጣንም “የቁጩ”
ባይሆን ኖሮ ምድር የሚበቃዎት አይመስለኝም፡፡ አቶ
መለስም መተካካት በሚል ለፈጠሯት የሥልጣን ዕድሜ
ማራዘሚያቸው ከ2002 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ርስዎ ብርሃንዋ
በደበዘዘ ባትሪ ተፈልገው ተገኙ፡፡ “ከአብሮ አደግ አትሰደድ”
በሚል ውስጠ ሚስጥር የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ
የመጣውን ጀግናውን የህወሓት ሠራዊት በዘዴ የሸኙት
አቶ መለስ በሁለት አስርት አመታት አገዛዛቸው የትግል
አጋሮቻቸውን በሰበብ በአስባቡ ከጨዋታ ውጭ እያደረጉ
በሥልጣን መንበራቸው ዙሪያ ከኮለኮሏቸው ጋሻ ጃግሬዎች
እንደ ጆከር እየተሰኩ የፖለቲካውን ቁማር የሚያስቆምሩ
በመሆንዎ፡፡
ክቡር ም/ጠቅላይ ሚ/ርና የውጭ ጉዳይ ሚ/ር
የሲዳማ ብሔር ተወላጆች የሆኑት አቶ አባተ ኪሾና አቶ
ሽፈራው ሽጉጤ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች
ክልል ፕሬዝዳንት ሆነው ክልሉን ሲመሩ ርስዎ ለበለጠዉ
ቦታ በአቶ መለስ ተቀቡ፡፡ የደቡብ የሹመቱ ተራ ከሲዳማ
ብሔረሰብ ወደ ወላይታ አመራ፡፡ በወቅቱ ሁኔታው በክልሉ
የበላይነት ስሜትን ለሚያንፀባርቁና በአንዳንድ አራዳዎች
አባባል “የደቡብ ትግሬዎች” የሚል ስም ለተሰጣቸው
የሲዳማ ብሔረሰብ ሹማምንት የእርስዎ ፕሬዝዳንት
መሆን አልተዋጠላቸውም ነበር፡፡ ውስጥ ውስጡን እያየለ
የመጣው ሽኩቻ ውሎ አድሮ ችግር መፍጠሩ አልቀረም፡፡
የደቡብ ክልል በጉያዋ ካቀፈቻቸው ከ56 በላይ ብሔረሰቦች
መካከል የሲዳማና የወላይታ ብሔረሰብ ተወላጆች
ቁጥራቸው የላቀ እንደሆነ ይታመናል፡፡ የወላይታ ህዝብ ግን
ስፋት ባለው የመሬት ይዞታ ላይ አለመስፈሩ ይታወቃል፡፡
የክልሉን የፕሬዝዳንትነት ሥልጣን ያጡት የሲዳማ
ተወላጅ ሹማምንት በምርጫ 97 ዓ.ም ዋዜማ ላይ በብርቱ
አጉረመረሙ፡፡ መልክአ ምድራዊ አቀማመጣቸውንና
የህዝባቸውን የቁጥር ብዛት አንተርሰው ራሳቸውን ችለው
ክልል ለመሆን ለፌደራል መንግስት ጥያቄ አቀረቡ፡
፡ በወቅቱ የሲዳማ ዞን ዋና ከተማ ከሀዋሳ ተነስቶ ወደ
ይርጋለም ከተማ መዛወሩና ሀዋሳ የደቡብ ህዝቦች ክልላዊ
መንግስት ርዕስ ከተማ መሆኗ የሲዳማን ህዝብ በብርቱ
እንዳስከፋው ይታወቃል፡፡ ውድ አንባብያን በ1997 ዓ.ም
ምርጫ ቅንጅት አዲስ አበባ ላይ በማሸነፉ የኦሮሚያ ክልላዊ
መንግሥት ዋና ከተማ ከአዳማ አዲስ አበባ እንደመጣና
ሕዝቡ በየአካባቢው የድጋፍ ሰልፍ እንዲወጣ መደረጉ
ይታወቃል፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ከምርጫው
በፊት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት መቀመጫው ወደ
አዳማ ሲዛወር በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚገኙ የብሔረሰቡ
ተወላጆች ድርጊቱን በመቃወማቸው ብዙ አፍላ ወጣቶች
የጥይት ራት ሆነዋል፤ ብዙዎቹ ታስረዋል፤ የቀሩትም
ከአገር ተሰደዋል፡፡ ይህን ግፍ የፈፀመው ኢህአዴግ አይኑን
በጨው አጥቦ “አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ በመሆኗ
ህዝቡ ለኢህአዴግ ያለውን ድጋፍ በደስታ ገለፀ” ሲል ነጋሪት
አስጎሰመ፡፡ የታሪክ ማፈሪያ!
ወደ ዋናው ጉዳዬ ስመለስ በወቅቱ የነበረው የሲዳማ
ብሔረሰብ ተወላጆች ኩርፊያ አቶ መለስን ሁለት ጊዜ
ወደ ሀዋሳ አመላለሳቸው፤ ጥያቄው ለሕወሓት ዘዋሪው
ኢህአዴግ ለአፍታ እንኳን የማይዋጥ ጉዳይ በመሆኑ
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ በአጭሩ መቀጨት ነበረበት፡፡
በመጀመሪያው ዙር ድርድር ራሳቸውን ችለው ክልል መሆን
እንደማይችሉ አስረግጠው የነገሯቸው አቶ መለስ “ለህፃን
ልጅ ብርጭቆ አይሰጥም” ሲሉ ቅስማቸውን በመስበር
አሸማቀቋቸው፡፡ ይሁን እንጂ የተቀጣጠለው እሳት ሙሉ
ለሙሉ አልጠፋም ነበር፡፡ ችግሩ እንደገና አገርሽቶ ሕዝቡ
ተቃውሞ በመውጣቱ አያሌ የሲዳማ ብሔረሰብ አባላት
ከአኝዋክ ህዝብ ባልተናነሰ ሁኔታ መጨፍጨፋቸው
የሚዘነጋ አይደለም፡፡ አቶ መለስም ከሁኔታዎች አሳሳቢነት
የተነሣ ዳግም ሀዋሳ ከተማ ተገኙ፤ እንደ ቀድሞው
ተለሳልሰው ሳይሆን እሳት ጎርሰው እሳት ለብሰው አመፁን
በቀዳሚነት የመሩትን የሲዳማ ብሔረሰብ ሹማምንትና ጋሻ
ጃግሬዎቻቸውን ከስልጣናቸው አራግፈውና የሲዳማ ዞንን
ዋና ከተማ ወደ ሀዋሳ እንዲመለስ መመሪያ ሰጥተው ካረጋጉ
በኋላ “ምጣዱ መስማቷ ላይቀር እንጨት ትጨርሳለች፡፡”
ሲሉ ተሳለቁባቸው፡፡ እንቅስቃሴውን ለአንዴና ለመጨረሻ
ጊዜ ለማዳፈንም አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝን አንስተው
ለሁለተኛ ጊዜ አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ሾሙ፡፡ መንበር
ስልጣኑ ከወላይታ ወደ ሲዳማ ሲመለስ ነገሮች ፀጥ ረጭ
አሉ፡፡

የበለጠውን በምቀጥለው ሊንክ ያንቡ:
http://andinet.org/wp-content/uploads/2012/03/Finote-Netsanete-Issue-35.pdf

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa