Skip to main content

በሐዋሳ በተነሳው የእሳት አደጋ ንብረት አወደመ: በሐዋሳ ከተማ የንግድ ተቋማት ባለንብረቶች: ከኢንሹራንስ ይልቅ ማኅበራዊ ተራድኦን የሚመርጡ መሆናቸው ተነገረ


 በአደጋው የከተማው አስተዳደር እሳት አደጋ መከላከል አቅም ተፈትሿል
መጋቢት 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ በሐዋሳ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በሁለት መደብሮች የተነሳው እሳት ንብረት አወደመ:: ወደ ክብሩ ሆስፒታል መሄጃ ላይ እየሩሳሌም የጨርቃ ጨርቅ መደብርንና አጠገቡ ያለው ጥሩወርቅ የኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት በእሳቱ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን፣ ባለንብረቶቹ እንደሚሉት 1.3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በተነሳው እሳት የእሳት አደጋ መከላከያ በወቅቱ ባለመድረሱና ዘግይቶ ከደረሰም በኋላ አቅሙ ውስን በመሆኑ፣ በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት ማዳን እንዳልተቻለ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ እንደ እማኞቹ አስተያየት ያለምንም መከላከያ ለ20 ደቂቃዎች ያህል ሲቀጣጠል የነበረው እሳት፣ በመደብሮች ውስጥ የነበሩትን ጨርቃ ጨርቆችና ኮምፒውተሮች በፍጥነት ጋይተዋል፡፡

የእየሩሳሌም ጨርቃ ጨርቅ መደብር ባለቤት አቶ ጌቱ ደምቦባ ስለደረሰው ጉዳት ተጠይቀው፣ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጣቃዎችና የተዘጋጁ ልብሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸው፣ የእሳቱን መንስዔ በተመለከተ ለተጠየቁት ሲመልሱ፣ ማናቸውንም የኤሌክትሪክ ዕቃዎችንና ካውያዎችን በአግባቡ ካጠፉ በኋላ መደብራቸውን መዝጋታቸውንና እሳቱ ከየት እንደተነሳ እንደማያውቁ ለሪፖርተር ጠቁመዋል፡፡ የጥሩወርቅ ኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት ባለቤት በበኩላቸው፣ ከ300 ሺሕ ብር በላይ የሚገመቱ ኮምፒውተሮችና የፎቶ ኮፒ ማሽኖች እንዲሁም የስቴሽነሪ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸዋል፡፡

በምሽቱ የተፈጠረውን እሳት ለመከላከል የሐዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የእሳት አደጋ መከላከያና የከተማው የእሳት አደጋ መከላከያ በአጠቃላይ ሦስት ተሽከርካሪዎችን በማሳተፍ ባደረጉት ርብርብ፣ ከምሽቱ 2፡30 ሰዓት አካባቢ እሳቱ ሙሉ በሙሉ ሊጠፋ ችሏል፡፡ 28 ቀበሌዎች ያሉት የሐዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሁለት የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎች ውኃ ስላልነበራቸው እሳቱ በተነሳ ጊዜ ከሐዋሳ ሐይቅ እየተመላለሱ ሲቀዱ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በከተማዋ ከዚህ ቀደም በአቶቴ ካፌና ሬስቶራንት ተመሳሳይ የእሳት አደጋ ተከስቶ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ በሐዋሳ ከተማ የንግድ ተቋማት ባለንብረቶች ከኢንሹራንስ ይልቅ ማኅበራዊ ተራድኦን የሚመርጡ መሆናቸውን የሚገልጹ አንድ የኢንሹራንስ ባለሙያ፣ የእሳት አደጋ መከላከያ አቅም ውስን በሆነበት በአሁኑ ጊዜ፣ የመድን ዋስትና ጠቀሜታ ቦታ ሊሰጠው ይገባል ሲሉ ለሪፖርተር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ 

በሌላ ዜና በሐዋሳ ከተማ የተከሰተው የስኳር እጥረት ከፍተኛ ችግር እንደፈጠረባቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ ባሉት የችርቻሮ መደብሮች ስኳር በኪሎ ማግኘት እንደማይቻል፣ ከተገኘ ደግሞ በድብቅ እስከ 30 ብር የሚሸጥ መሆኑንና አብዛኛውን ጊዜ በችርቻሮ ብቻ እንደሚሸጥ ነዋሪዎች በምሬት እየተናገሩ ነው፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa