Skip to main content

በደቡብ ክልል የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጠናከር የተጀመረው የለውጥ አሰራር መሻሻል አሳይቷል

የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ጉዬ በበኩላቸው በስራቸው በሚገኙ 19 ወረዳዎችና ሀዋሳን ጨምሮ በሁለት የከተማ አስተዳደሮች አዲሱ የለውጥ አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል
ሃዋሳ, ጥር 5 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክልል የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበትና ለማጠናከር የተጀመረው የለውጥ አሰራር መሻሻል ማምጣቱን አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችና ባለጉዳዮች ገለጹ፡፡
ዘንድሮ በክልሉ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ሰዎች የህግ ግንዛቤ የሚያሳድግ ትምህርት እንደሚሰጥም ተመልክቷል፡፡
የክልሉ ፍትህ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል እንዳሻው ስመኖ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ተከትሎ የመጣው አዲሱ የውጤት ተኮር የምዘና ስርዓት ፕሮግራም በክልሉ ከፍተኛ ለውጥ አምጥቷል፡፡
በዚህም ቀደም ሲል ፍርድ ቤቶች፣ ዐቃቢያነ ህግ፣ ማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ በተናጠል የሚያካሄዱትን የተበታተነ አሰራር በማስወገድ በአንድ ላይ ተቀናጅተው እንዲሰሩ ተደርጓል ብለዋል፡፡
በተለይ የምርመራና የክስ፣ የህግ ጥናት ረቂቅ ዝግጅትና ግንዛቤ መፍጠር፣ የጠበቆችና ሲቪክ ማህበራት ፍቃድ ውልና ምዝገባ ክትትል ከተገኙት ለውጦች መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን አመልከተዋል፡፡
በዚህም የፍትህ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ቀደም ሲል ከስድስት ወር በላይ የሚፈጀው አሁን በሰዓታት፣ በቀናት ቢበዛ እስከ አንድ ወር ባለው ጊዜ ውሳኔ እያገኙ ናቸው ብለዋል፡፡
ከወንጀልና ከፍትሃብሄር ክሶች ጋር ተያይዞ ንፁሃን እንዳይጎዱና አጥፊዎች እንዳያመልጡ የተቀመጠው ግብም ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የፍትህ አካላቱ ተቀናጅተው መስራታቸው ፈጣን ፍትህ ለተጠቃሚው ለመስጠት ትልቅ አቅም መፍጠሩን አስረድተዋል፡፡
እንዲሁም በአዲሱ አሰራር ከሶስት ዓመት በታች የሚያሳስሩ መለስተኛ የወንጀል ድርጊቶች በእርቅ እንዲፈቱ የተጀመረው ፕሮግራም ህብረተሰቡ ከልማት ስራዎቹ እንዳይገታ፣ አላስፈለላጊ የመዝገብ ክምችት እንዳይኖርና የፈፃሚዎችን ጊዜ ለመቆጠብ ማስቻሉን ጠቁመዋል፡፡
ፍትህን ተደራሽ ከማድረግ አኳያ በተለይ ቀደም ሲል የነበረው የተዘዋዋሪ ችሎት ወደ ምድብ ችሎት በመቀየር እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ ተደራጅተው አፋጣኝ ውሳኔና ምላሽ በመስጠት ህብረተሰቡ ተጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ጉዬ በበኩላቸው በስራቸው በሚገኙ 19 ወረዳዎችና ሀዋሳን ጨምሮ በሁለት የከተማ አስተዳደሮች አዲሱ የለውጥ አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ተጨማሪ ምድብ ችሎቶች በአለታ ወንዶና በይርጋዓለም ዳሌ ተዘዋዋሪ ችሎት በመክፈት የመዝገብ ክምችቶችና ውጣ ውረዶችን መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
በሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትና በሀዋሳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከተገኙት ባለጉዳዮች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት የፍርድ ቤቶቹ አገልግሎት አሰጣጥ ከቀድሞው ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው፡፡
በተጨማሪም በክልሉ ዘንድሮ የህብረተሰቡን የህግ ግንዛቤ ለማሳደግ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የተለያዩ የብዙሃን መገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም ትምህርት ለመስጠት እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ ፍትህ ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አመልክተዋል፡፡
ይህም ዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብታቸው ተከብሮላቸው ግዴታቸውን እንዲወጡ፣ የፍትህ ስርዓቱ እንዲጎለብትና እንዲጠናከር የህብረተሰቡ ተሳትፎና ግንዛቤ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa