Skip to main content

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በአሲዳማ አፈር ላይ ከፍተኛ ምርት ማግኘት እንደሚቻል በምርምር ማረጋገጡን አስታወቀ


አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 26 2004 /ዋኢማ/ -የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በአሲዳማ አፈር ላይ የቢራ ገብስና የስንዴን ምርት ለማሳደግ ላለፉት አራት አመታት ሲያካሂድ በቆየዉ ምርምር በሄክታር ከአምስት እጥፍ በላይ ምርት ማግኘት እንደሚቻል ማረጋገጡን አስታወቀ፡፡
ዩኒቨርስቲው በአሁኑ ወቅት ከ100 የሚበልጡ የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ መሆኑም ተመልከቷል፡፡
የዩኒቨርስቲው የምርምር ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋዬ አበበ በሲዳማና በጌዴኦ ዞኖች መልጋና ቡሌ ወረዳዎች ሰሞኑን በተካሄደ የመስክ ጉብኝት ላይ እንደተናገሩት አሲዳማ አፈርን ምርታማ ማድረግ የተቻለው በአርሶ አደሩ ማሳና በገበሬ ማሰልጠኛ ማዕከላት በተከናወነ በተግባር የተደገፈ የሙከራ ምርምር ነው ።
አርሶ አደሩን በማሳተፍ ሲከሄድ በቆየዉ በዚሁ ምርምር አሲዳማ አፈርን ከኖራ ፣ ተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ ጋር አቀናጅቶ በማከም የቢራ ገብስን በሄክታር እስከ 34 ኩንታል በማምረት በተለምዶ ከሚገኘው ከ5 እጥፍ በላይ ምርት መገኘቱን ገልፀዋል ።
በስንዴ ምርት ላይ በተካሄደ ምርምርም በተመሳሳይ ከፍተኛ ምርት ሊገኝ መቻሉን ዶክተር ተስፋዬ አስታውቀዋል፡፡
በሲዳማ ፣ በጌዴኦ ፣ በስልጤና ጉራጌ ዞኖች በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች የምርምር ስራው የተካሄደው ከኔዘርላንድ መንግስትና ከሌሎች የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በምርምር ስራው ላይ ከ200 የሚበልጡ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውንና ምርምሩ እስከቀጣዮቹ አምስት አመታት እንደሚቆይና የተሳታፊ አርሶ አደሮችን ቀጥርም ከአራት ሺህ በላይ ለማድረስ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው።
የምርምሩ ዋነኛ አላማም የገበሬውን ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር መሆኑን የምርምር ልማቱ ዳይሬክተር አስረድተዋል፡፡
የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በበኩላቸው ከመማር ማስተማሩ ጎን ችግር ፈቺና ህብረተሰብ አሳታፊ የሆኑ የምርምር ስራዎችን ለማስፋፋት ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮች ተቋቁመው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድን ለማሳካት እየሰሩ መሆናቸዉን ተናግረዋል ።
ከምርምሩ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል በሲዳማና ጌዴኦ ዞኖች መልጋና ቡሌ ወረዳዎች የሚገኙት አርሶ አደር ደስታ ዳሌና ጎበና አአሎ በሰጡት አስተያየት ቀደም ሲል ከአሲዳማ አፈር ላይ በሄክታር ያገኙት የነበረዉን ከአራት ኩንታል በታች ምርት በምርምሩ በብዙ እጥፍ በማሳደግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በደቡብ ክልል በተመረጡ ስድስት አካባቢዎች ከ100 በላይ ችግር ፈቺ የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ መሆኑን ዶክተር ተስፋዬ አመልክተው የምርምር ስራዎቹም በግብርና ፣ በተፈጥሮ ሀብት ፣ በደን ልማት ፣ በእንስሳት ፣ በጤና ፣ በትምህርትና በሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች ላይ ማተኮሩን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa