Skip to main content

የኢትዮጵያ ዋነኛ ቡና ገዥዎች ለመንግሥት ተቃውሟቸውን አሰሙ


-    ቡና ላኪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አቤቱታ ሊያቀርቡ ነው

የኢትዮጵያ ቡና ገዥ ከሆኑት መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱት የስዊዘርላድንና የጀርመን ኩባንያዎች በማኅበሮቻቸው በኩል ለኢትዮጵያ ኤምባሲዎች፣ ለውጭ ጉዳይና ለንግድ ሚኒስቴር የተቃውሞ ደብዳቤ መጻፋቸው ታወቀ፡፡
የእንግሊዝ ኩባንያዎችን ጨምሮ አሥር ታዋቂ የኢትዮጵያን ቡና የሚገዙ ማኅበራት በብትን እንደማይገዙ ያሳወቁ ሲሆን፣ ፊታቸውን ወደ ሌሎች ቡና ሻጮች ማዞራቸውም እየተነገረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የኮሎምቢያና የኬንያ ቡና ላኪዎች የአረቢካ ቡና ገበያን ሊቆጣጠሩት እንደቻሉ፣ በዚህ ሳምንት ብቻ ኢትዮጵያ ልትሸጥ የሚገባት 30 ሺሕ ቶን የሚገመት ቡና ሳይሸጥ መቅረቱን ምንጮች ይናገራሉ፡፡

ንግድ ሚኒስቴር ከህዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ያወጣው መመርያ ቡና ገዥዎች እንደተቃወሙትና በኮንቴይነር በብትን እንዲላክልን አንፈልግም ብለውናል በማለት የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ያቀረቡትን ሐሳብ ሚኒስቴሩ ሊቀበለው ባለመቻሉ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአቤቱታ ደብዳቤ ለማቅረብ መገደዳቸውንና በነገው ዕለትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት እንደሚያስገቡ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ከህዳር 1 ቀን ጀምሮ ሁሉም ላኪዎች ቡና በብትን በኮንቴይነር እንዲልኩ የወጣውን መመርያ ቡና ገዥዎች እንዳልተቀበሉት፣ በጆንያ የማይላክላቸው ከሆነ ከኢትዮጵያ ቡና አንገዛም ማለታቸውን ለሚኒስቴሩ ቢያሳውቁም፣ ሳይቀበላቸው በመቅረቱ አሳምናችሁ በብትን እንዲገዙ አድርጉ በማለት ኃላፊነቱን ጥሎባቸዋል፡፡

ከፍተኛ የታጠበ ቡና በጥርና በካቲት ወራት ተጓጉዞ ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ አሁን ውል ሊፈጸም ይገባ እንደነበር የሚገልጹት ቡና ላኪዎች፣ አሁን በሚታየው የዓለም የኢኮኖሚ መዋዠቅ የቡና ኤክስፖርት መቀነሱን ይናገራሉ፡፡ ገዥዎች እምቢ ከማለታቸው ጋር ተያይዞ ቡናው በመጠንና በገቢ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን፣ ወደፊትም ከዚህ የበለጠ ሊቀንስ እንደሚችልና የአገሪቱን የወጪ ንግድ ገቢ እጅግ የሚጎዳ አሳሳቢ ችግር መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡

ሆኖም አንዳንድ ላኪዎች በብትን እየላኩ እንደሚገኙ፣ ጥቂቶችም መመርያውን ወደ ጎን በማለት በጆንያ እየላኩ መሆኑን፣ ይህን በማድረጋቸው የሚደርስባቸው ነገር ካለም ‹‹የሚመጣውን ለመቀበል ተዘጋጅተናል›› የሚሉ አልጠፉም፡፡

‹‹የኢትዮጵያ ቡና ራስን በራስ የማጥፋት ዕርምጃ ተወስዶበታል፤›› ሲሉ አንዳንድ  የቡና ላኪዎች የገለጹ ሲሆን፣ የንግድ ሚኒስቴር ያወጣውን መመርያ አስመልክቶ የተቃውሞ ፊርማ እየተሰባሰበ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa